• This is default featured slide 1 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 2 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 3 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 4 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 5 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

በረመዳን ምግብ የበሉ 80 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ናይጄሪያ፡ በረመዳን ምግብ የበሉ 80 ሰዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ


የረመዳን ምግብImage copyrightGETTY IMAGES

በናይጄሪያዋ ካኖ ግዛት በረመዳን ጾም ወቅት በአደባባይ ምግብ የበሉ 80 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የግዛቲቱ እስላማዊ ሸሪያ ፖሊስ አስታውቀ።
ሂስባህ የሚል ስያሜ ያላቸው እነዚህ የሸሪያ ፖሊሶች በግዛቲቱ በተለያዩ አካባቢዎች ባለፉት ቀናት ቁጥጥር ሲያደርጉ ነው ግለሰቦቹን የያዙት።
በፈረንጆቹ 2000 የሸሪያ ህግ እንደገና ተግባራዊ ከተደረገባቸው በርካታ የናይጄሪያ ግዛቶች መካከል አንዷ በሆነችው ካኖ ግዛት የሚኖሩ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ጸሃይ ወጥታ እስትክጠልቅ ድረስ ምግብ በአፋቸው እንዳይዞር ህጉ ያዛል።
የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ያልሆኑ ሰዎች በቤታቸው እንደፈለጉት መመገብ የሚችሉ ሲሆን የእስልምና ተከታዮች ግን በጾም ወቅት በአደባባይ መመገብ አይችሉም።
በግዛቲቱ የሸሪያ ህጉም ከመንግሥታዊ ህጉ ጋር ጎን ለጎን በመሆን ይሰራል።
በካኖ ግዛት የሂስባህ ቃል አቀባይ የሆኑት አዳሙ ያህያ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በአደባባይ በመመገባቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት ሁሉም ሙስሊሞች ሲሆኑ የሸሪያ ህጉ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ያልሆኑት ላይ ተግባራዊ አይሆንም።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል አንዳንዶቹ ምግብ የበሉት የረመዳን ጨረቃን እራሳቸው ባለማየታቸው እንደሆነ ሲገልጹ፤ ሌሎቹ ደግሞ የጤና እክልን እንደ ምክንያትነት ቢያቀርቡም ባለስልጣናቱ ግን ተቀባይነት የሌለውና ምክንያት ነው ብለዋል።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ሰማንያዎቹ ግለሰቦች ተግባሩን ሲፈጽሙ የመጀመሪያቸው በመሆኑ በከባድ ማስጠንቀቂያ መለቀቃቸውን ቃል አቀባዩ አክለዋል።
ከዚህ በኋላ በረመዳን ወቅት ከማፍጠሪያ ሰዓት ውጪ ምግብ ሲበሉ ቢገኙም ወደ ፍርቤት ተወስደው ለመዳኘት ቃል ገብተዋል።
የሂስባህ አባላቱም በረመዳን የጾም ቀናት ከተማዋን በማሰስ ተመሳሳይ ተግባር የሚፈጽሙ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን እንደሚቀጥሉበትም ተገልጿል።
Share:

በጦላይ የኦነግ ሠራዊት አባላት ላይ የተከሰተው ምንድን ነው ?

ከባለፈው እሁድ ጀምሮ የጤና እክል ገጥሟቸው ሆስፒታል እየገቡ ያሉ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ወታደሮች ቁጥር እየጨመረ ነው።
ወታደሮቹ ቁርስ ተመግበው ሲነሱ ብዙ እራሳቸውን እየሳቱ መውደቅ መጀመራቸው መነገሩ ይታወሳል። ወታደሮቹ ጨምረውም የቀረበላቸው ሻይ ውስጥ ነጭ ባዕድ ነገር መመልከታቸው እና የተለየ ጠረን እንዳለው ጨምረው ተናግረዋል።
"ሻይ በምንጠጣበት ብርጭቆ ስር ነጭ ዱቄት የሚመስል ነገር አግኝተናል፤ ይህንንም ለማሰልጠኛው አስተዳደሮች አሳይተናል" ሲል አንድ ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ የኦነግ ሠራዊት አባል ለቢቢሲ ተናግሯል።
የጤና እክል በገጠማቸው የሠራዊቱ አባላት ላይ የሚታዩበት ምልክት ምን እንደሆነ ሲናገር "የአፍ ድርቀት፣ የሆድ ቁርጠት፣ ሆድ የማቃጠል ስሜት፣ ከደም ጋር የተቀላቀለ ትውከትና የፊት መገርጣት ናቸው" ብሏል።
የኦሮሚያ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር የሆኑት ረታ በላቸው፤ በጦላይ በሚገኙ የኦነግ ወታደሮች ላይ ያጋጠመው የጤና ችግር መንስዔ እየተጣራ ነው ያሉ ሲሆን የደረሰባቸው የጤና እክል ግን ለህይወት አስጊ አይደለም ብለዋል።
እንደ ምክትል ኮሚሽነሩ ከሆነ 134 የኦነግ ወታደሮች በወሊሶ ቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደነበር ተናግረዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ የጦላይ ማሰልጠኛ አስተዳደሮች ጉዳት አስከተለ የተባለውን ሻይ ቀምሰው ምን የደረሰባቸው ነገር የለም ብለዋል። ''እኛ የቀረበላቸው ሻይ ውስጥ መርዝ ተጨምሯል ብለን አናምንም፤ ምርመራ እየተካሄደ ነው። እንደተባለው መርዝ ተጨምሮ ከተገኘ ግን ጠፋተኛው ላይ እርምጃ ይወሰዳል።''
በዚሁ ሆስፒታል እየታከመ የሚገኘው ሌላኛው የሠራዊቱ አባል ኢብሳ በበኩሉ የተሰጣቸውን ሁሉ ተመግበው ቢሆን ኖሮ ጉዳቱ ከፍ ያለ ሊሆን እንደሚችል ገልፆ "ሁላችንም እናልቅ ነበር" በማለት ተናግሯል።
"ይሄ ነገር የመርዝ ሽታ አለው ብዬ ስላስቆምኩዋቸው ሻዩን አልጨረሱትም ነበር። ገሚሱ ቀምሰው ብቻ ስለሆነ የተዉት በዚያ መንገድ ነው የተረፍነው" ይላል።
"እከሌ ብለን ማንም ላይ ጣታችንን ባንቀስርም ህብረታችንን የማይወዱ ሰዎች እንዳሉ እንጠረጥራለን። ነገር ግን ግቢው ውስጥ ካሉ ሰዎች ጋር ምንም አይነት ግጭት የለንም" ብሏል።
ወሊሶ በሚገኘው የቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል ሃኪም የሆኑት ዶ/ር አብዱላቲፍ ይሲያቅ እስከ ዛሬ ማክሰኞ ከሰዓት ድረስ 154 የኦነግ ሠራዊት አባላት ህክምና እየተደረጋለቸው መሆኑን ተናግረዋል።
"በእኛ ምርመራ መሰረት የምግብ መበከል (መመረዝ) ሳይሆን ራሱን የቻለ መርዝ ተጨምሮበት እንደሆነ ነው የሚያሳየው። የሠራዊቱ አባላትም መርዝ እንደሸተታቸው ተናግረዋል" ብለዋል።
ዶ/ሩ ጨምረውም ታካሚዎች ራስ ምታት፣ የሆድ ቁርጠት፣ ሆድ የማቃጠል ስሜት፣ ከደም ጋር የተቀላቀለ ትዉከትና የፊት መገርጣት ምልክቶች እንደታየባቸው በመናገር እነዚህም የመርዝ ምልክቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።
የክልሉ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው በበኩላቸው 136 የኦነግ ሠራዊት አባላት በጤና እክል ምክንያት በወሊሶ ሉቃስ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑንና የከፋ የጤና ችግርም እንደሌለ ለመንግሥት ሚዲያዎች በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
በመግለጫቸው ጨምረው በሠራዊቱ አባላት ላይ የምግብ መመረዝ ደርሶባቸዋል፤ ሠራዊቱ ላይም ይህ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው እየተባለ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው ብለዋል።
ያጋጠመውን የጤና እክል መንስኤም ለማጣራት ፖሊስና የሚመለከታቸው አካላት ምርመራ እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀው መንስኤውም ሲታወቅ ውጤቱ ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ነው
Source 
bbc
Share:

በወሲብ ፊልሞች ሱሰኛ የሆኑ ወጣት ሴቶች

ኔላም ቴለር የወሲብ ፊልሞችን ማየት የጀመረችው በ12 ዓመቷ ነበር። ገና አንድ ፍሬ ልጅ በምትባልበት ጊዜ። በመኝታ ክፍሏ ተደብቃ አጠር ያለ የአስር ደቂቃ የወሲብ ፊልም ማየት የጀመረችው በለጋ እድሜዋ ነው።

ኋላ ላይ እስከ አንድ ሰዓት ርዝማኔ ያላቸው ምስሎችን ማየት ጀመረች። በጊዜው ከቤተሰቦቿ ተደብቃ ታይ እንደነበር የምትናገረው ኔላም ለመጀመሪያ ጊዜ የወሲብ ፊልም ስታይ "የፍቅር ፊልሞች ወሲብን የተቀደሰና በፍቅር የተሞላ አድርገው ነበር አዕምሮዬ ላይ የሳሉት፤ ልክ በወንዶች ሃያልነት የተሞላና አካላዊ ተራክቦው የጎላበትን ምስል ማየት በጣም ነው ያስደነገጠኝ" ትላለች።
የወሲብ ምስሎችን ማየት የጀመረችበትን ሰበብ ስታስታውስ ጉዳዩን ለማወቅ ከነበራት ፍላጎት ወይም ለአቅመ-ሔዋን እየደረሰች ስለነበረ የአፍላ ጉርምስና ግፊት ይሆናል በማለት ትናገራለች።
ከጊዜ በኋላም የተለያዩ የወሲብ ምስሎችን ከማየቷ የተነሳ የራሷ ምርጫዎች እያዳበረች መጣች።
"ወጣት ሴቶች በዕድሜ ገፋ ካሉ ወንዶች ጋር ሆነው ለሚሰሩ የወሲብ ምስሎች ልዩ ስሜት አደረብኝ። ሴቶቹ ታዛዥ ሆነው ወንዶቹ የበላይ የሆኑባቸውን ምስሎች በ13 ዓመቴ መፈለግ ጀመርኩ" የምትለው ኔላም ይህ ፍላጎቷ ብዙ የወሲብ ምስል ከማየቷ የተነሳ ይሁን ወይም ተፈጥሯዊ የሆነ ስሜት መለየት ይከብዳታል።
የ25 ዓመቷ ሳራም ከኔላ የተለየ ልምድ የላትም። የወሲብ ምስሎችን ማየት የጀመረችው በ13 ዓመቷ ነበር፤ ለዚያውም በሳምንት ሁለት ጊዜ። 
እስካሁን የወሲብ ምስል ሱስ በወንዶች ላይ የሚያደርሰው ተፅዕኖ በደንብ የተጠና ሲሆን፤ በሴቶች ላይ ያለው ጫና ግን በውል አልተጠናም። ብዙ በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ ባለሙያዎች ሴቶች የወሲብ ምስልን እንደሱስ እንደማይጠቀሙትና በእነርሱ ላይ ብዙም ተፅዕኖ እንደሌለው ይናገራሉ። በዚህ የሕይወት መንገድ ላይ ያለፉ ሴቶች ግን ተመሳሳይ መልስ አይሰጡም።
ዶ/ር ለይላ ፈሮድሻ የፅንስና የማህፀን አማካሪ ስትሆን በ20 ዓመት የስራ ልምዷ "አንድም የማያቸው የወሲብ ምስሎች ችግር እየፈጠሩብኝ ነው" ብላ የመጣች ሴት አጋጥማት እንደማታውቅ ትናገራለች።
በጉዳዩም በደንብ ጥናት እንዳልተደረገበት የምትናገረው ለይላ "ሴቶች አካላዊና ስለ ልቦናዊ ጥቃት እየደረሰባቸው ነገርግን የሐኪም እርዳታ እየጠየቁ ስላልሆነ ነው? ወይስ ስለደረሰባቸው ችግር ለመናገር አፍረው? ወይስ ምንም ችግር እየፈጠረባቸው አይደለም?" በማለት ያልተመለሱ ጥያቄዎችን ታቀርባለች።
ኔላም 16 ዓመቷ ሲሆን የወሲብ ምስሎችን ማየት አቆመች፤ ለዚህ ደግሞ ሰበብ የሆናትን ስትጠቅስ ምስሎቹ ተፈጥሯዊ ያልሆነ ከፍተኛ ስሜት ውስጥ ስለሚከቱ ነው ትላለች። ከእውነታው እያራቀች እንደነበር የምትገልፀው ኔላም "የወሲብ ምስል አይቼ የማገኘው የስሜት እርካታና ከጓደኛዬ ጋር ከወሲብ በኋላ ያለኝ ስሜት ያላቸው ልዩነት ያስፈራኝ ነበር።"
አሜሪካዊቷ ፀሃፊ ኤሪካ ጋርዛ የወሲብ ምስል ማየት የጀመረችው በ12 ዓመቷ እንደሆነ ስትናገር "ትምህርት ቤት ያላግጡብኛል፤ ብዙ ጊዜም ብቸኛ ነበርኩ። ስለዚህም የወሲብ ምስሎችን ችግሬን የምረሳበትና እራሴን የማስደስትበት ነገር ነበር" ትላለች።
ኔላምም በተመሳሳይ መልኩ የወሲብ ምስሎችን በለጋ ዕድሜዎ ማየቷ ወሲብን የምታይበትን መንገድ እንደቀየረው ትናገራለች።
" 17 ወይም 19 እድሜዬ ላይ ስደርስ ታላቆቼ ከሆኑ ጋር ግንኙነት መፍጠር ጀመርኩ። ይህ ሁኔታዬ የተፈጥሮ ባህሪዬ ይሁን የወሲብ ምስል ማየቴ የፈጠረው ለማወቅ አልችልም" ትላለች።
እ.ኤ.አ በ2010 በተደረገ የ300 የወሲብ ምስሎች ግምገማ 88 በመቶ የሚሆኑት አንዱ ፆታ በወሲብ ላይ ያለውን የበላይነትን የሚያመላክቱ ሲሆን ብዙዎቹም የወንዶች የበላይነት ናቸው። በምስሎቹም ሴቶቹ በወንዶቹ ባህሪ በደስታ ወይም ከስሜት ነፃ በሆነ መልኩ እንደሚመልሱ ያሳያሉ
Share:

አደጋው የደረሰበት ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን የገጠመው ምንድን ነበር?

ከሦስት ሳምንታት በፊት አደጋ ስለደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎች እየወጡ ነው።

በዚህም በቦይንግ 737 ማክስ ላይ ያለው አውሮፕላኑ ዝግ እንዳይል ወይም እንዳይቆም የሚያደርገው የአውሮፕላኑ ሥርዓት የ157 ሰዎችን ህይወት ለቀጠፈው አደጋ ምክንያት እንደሆነ እየተነገረ ነው።
አደጋው ከመድረሱ በፊት በሁለቱ አብራሪዎች መካከል የተደረገን ምልልስ ጠቅሶ ዎል ስትሪት ጆርናል እንደዘገበው፤ የአውሮፕላኑ የሬዲዮ ግንኙነት ከመቋረጡ በፊት አንደኛው አብራሪ "ቀና አድርገው! ቀና አድርገው!" በማለት ለባልደረባው ሲናገር ተሰምቷል።
በአውሮፕላኑ ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመቆጣጠር ያስችላል የተባለውን ሥርዓት አብራሪዎቹ ቢጠቀሙም አደጋውን ለማስቀረት እንዳልተቻለ እየተደረገ ላለው ምርመራው ቅርብ የሆኑ ምንጮች ለጋዜጣው ተናግረዋል።
አደጋ ከደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን የበረራ መረጃ መሰብሰቢያ ሳጥን ውስጥ ከተገኘ የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ መሰረት አደጋው ከመድረሱ በፊት እያሽቆለቆለ ያለውን አውሮፕላን ሊታደግ ይችላል የተባለው የአውሮፕላኑ ሥርዓት እንዲሰራ ተደርጎ እንደነበር አመልክቷል።
ዘ ዎል ስትሪት ጆርናል የተባለው ጋዜጣ ስለአደጋው የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት ስማቸው ያልተጠቀሱ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው የአውሮፕላኑ ከፍታና ዝቅታ ለመቆጣጠር እንዲያስችል ተደርጎ የተሰራው የኮምፒውተር ሥርዓት ችግር እንዳለው አመልክቷል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን የበረራ ቁጥር ኢቲ302 መጋቢት 1/2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ጠዋት 2፡38 በመነሳት ሁለት ሰዓት ብቻ ለሚፈጀው በረራ ወደ ናይሮቢ ፊቱን ቢያዞርም ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ችግር ገጥሞታል።
አውሮፕላኑ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከተነሳ ከስድስት ደቂቃዎች በኋላም 48 ኪሎሜትሮችን ከአዲስ አበባ በስተደቡብ ምሥራቅ ተጉዞ ከቢሾፍቱ አቅራቢያ ባለችው ቱሉ ፈራ መንደር ውስጥ ነበር ወድቆ የተከሰከሰው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላኑ ዋና አብራሪ ያሬድ ጌታቸው ችሎታን በተመለከተ አብራሪው ከ8ሺህ ሰዓታት በላይ የማብረር ልምድ እንዳለው በመጥቀስ "የሚያስመሰግን ብቃት" አለው ብሏል።
አደጋው በደረሰበት ዕለትም አብራሪው ያሬድ ጌታቸው ችግር እንደገጠመውና ተመልሶ ለማረፍ ለበረራ ተቆጣጣሪዎች መልዕክት አስተላልፎ ነበር።
ከዚህ አደጋ ጋር በተያያዘ የአውሮፕላኑ የደህንነት መጠበቂያ ሥርዓት ለሚደረገው ምርምራ ዋነኛው ጉዳይ ሆኗል


Image copyrighከዚህ አደጋ ጋር በተያያዘ የአውሮፕላኑ የደህንነት መጠበቂያ ሥርዓት ለሚደረገው ምርምራ ዋነኛው ጉዳይ ሆኗል።

ኤምካስ የተባለውና አውሮፕላኑን በከፍተኛ ሁኔታ ወደላይ እንዳይወጣ ወይም ወደታች እንዳያሽቆለቁል ለመቆጣጠር እንዲቻል ተብሎ የተሰራ ሥርዓት ነው።
በአውሮፕላኑ ዝግ ሲል በትክክለኛው አቅጣጫ እንዲበር ለማስቻል የሚፈለገውን ኃይል ለማግኘት ወደ ላይ ወይም ቁልቁል በመሄድ ወደሚፈለገው ከፍታ ይመለሳል። ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን በአውሮፕላኑ ክንፎች በኩል ያለውን የመቆጣጠሪያ አቅም በመቀነስ አውሮፕላኑ እንዲወድቅ ሊያደርገው ይችላል።
በተለመደው ሁኔታ አውሮፕላኑን ከዝግታ ለማውጣት አብራሪው የአውሮፕላኑ አፍንጫ ወደታች እንዲያዘቀዝቅ ያደርጋል። አደጋው በደረሰበት ቦይንግ 737 ማክስ አይነት አውሮፕላኖች ላይ ያለው የመቆጣጠሪያ ሥርዓት (ኤምካስ) ግን እንዲህ አይነቱ ሁኔታ ሲከሰት አውሮፕላኑን እራሱ አስተካክሎ ወደ ትክክለኛው ቦታ ይመልሰዋል።
አውሮፕላኑ ላይ ተመሳሳይ ነገር የሚከሰት ከሆነና ኮምፒውተሩ ይህንኑ ካወቀ የመቆጣጠሪያ ሥርዓቱ በተደጋጋሚ የማስተካከያ እርምጃን በእራሱ ይወስዳል።
በኢትዮጵያው አየር መንገድ ላይ አደጋው ከመድረሱ አምስት ወራት ቀደም ብሎ ተመሳሳይ አደጋ የደረሰበት የኢንዶኔዢያው አውሮፕላንም የበረራውን ማዕዘን በሚያሰላው የአውሮፕላኑ መቆጣጠሪያ ላይ ተመሳሳይ አይነት እክል ገጥሞት እንደነበር ተገልጿል።
በቦይንግ ምስለ በረራ ላይ በተደረገ ሙከራ እንደተረጋገጠው ኤምካስ የተባለው መቆጣጠሪያ ከሚጠበቀው በላይ ከበድ ያለ በመሆኑ በተደጋጋሚ የአውሮፕላኑ አፍንጫ ቁልቁል እንዲያዘቀዝቅ ያስገድዳል።
በኢንዶኔዢያው አውሮፕላን ላይ የደረሰውን አደጋ ለማወቅ በተደረገው የምስለ በረራ ሙከራ ላይ እንደተደረሰበት አውሮፕላኑ ቁልቁል በአፍንጫው ባህር ላይ ሊከሰከስ መሆኑን ያወቁት ከ40 ሰከንዶች ያነሰ ጊዜ ሲቀራቸው መሆኑን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል።
ይህንንም ተከትሎ ቦይንግ ኤምካስን እንዴት መጠቀም እንደሚቻል ለአብራሪዎች መመሪያ ቢያወጣም፤ ነገር ግን በአውሮፕላኑ ላይ ያለውን ሥርዓት የሚቆጣጠረው ሶፍትዌር ላይ ያስፈልግ የነበረው መሻሻያ ዘግይቶ ባለፈው ሳምንት ነው ይፋ የተደረገው።
በተጨማሪም በበረራ ወቅት ችግር በሚያጋጥም ጊዜ አብራሪዎችን ሊያስጠነቅቅ ይችል የነበረው የማስጠንቀቂያ መብራትም አደጋው በደረሰባቸው ሁለቱ የኢትዮጵያ እና የኢንዶኔዢያ አውሮፕላኖች ላይ አልተገጠመም ነበር።
ከሁለቱ አደጋው ከደረሰባቸው አውሮፕላኖች የተገኙ የበረራ መረጃዎች ተመሳሳይነት እንዳላቸው መርማሪዎች አመልክተዋል።
የአውሮፕላኖቹን ወደ ላይ የመውጣትና የመውረድ ፍጥነት ንባብ እንደሚያመለክተው ሁለቱም አውሮፕላኖች ከፍና ዝቅ እያሉ እንደነበሩና አብራሪዎቹም ይህንን በመቆጣጠር አውሮፕላኖቹ ከፍ ብለው እንዲበሩ ጥረት ሲያደርጉ ነበር።
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ የትራንስፖርት ደህንነት ቦርድ ጋር በመሆን ምርመራውን እያካሄደ የሚገኘው የአሜሪካ የአየር ትራንስፖርት ባለስልጣን እንዳለው ከአደጋው ስፍራና ከሳተላይት የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ሁለቱ አውሮፕላኖች ላይ በጣም የሚመሳሰሉ ነገሮች እንደታዩ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን የበረራ መረጃ መመዝገቢያውና የአብራሪዎቹ ክፍል ድምጽ መቅጃው ወደ ፈረንሳይ ተወስዶ ምርመራ ተደርጎበታል።

ምንጭ .bbc
Share:

ፌስቡክ የነጭ ብሔረተኝነትናና የተገንጣይ አመለካከት አራማጆችን ሊያግድ ነው

ፌስቡክ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ "የነጮችን ብሔርተኝነትና መለየትን የሚያሞግሱና የሚደግፉ" ፅሁፎችን ከፌስቡክና ከኢንስተገራም ገፆች ላይ እንደሚያግድ አሳወቀ።
ትልቁ የማህበራዊ ሚዲያ ፌስቡክ የሽብርተኝነት ይዘት ያላቸውን ይዘቶች ከድህረገፁ ላይ ለመለየትና ለማስወገድ እንደሚሰራም ቃል ገብቷል።
ቁጣን የሚቀሰቅሱ አባባሎችን የሚፈልጉ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች እንደዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ወደ የሚከላከሉ የበጎ አድራጎት ገጾች በመምራት ድግፍ እንዲያገኙ ያደርጋል።
በኒውዚላንድ የሁለት መስኪዶች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶች በቀጥታ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከተላለፈ በኋላ የማህበራዊ ሚዲያዎች ጫና በዝቶባቸዋል።
ፌስቡክ ከዚህ በፊት የነጮችን ብሔርተኝነት የሚያሳዩ ይዘቶችን እንደ ዘረኝነት ስለማይቆጥራቸው በገፁ ላይ እንዲገኙ ፈቅዶ ነበር።
"የአሜሪካ አክራሪ የነጮች ቡድንና በስፔን ያለው የባስክ ተገጣይ ቡድኖች አስፈላጊ የሰዎች ማንነት ክፍል እንደመሆኑት ሁሉ" የነጭ ብሔርተኝነትም ተቀባይነት ያለው እንደሆነ ይቀበል ነበር።
ነገር ግን ረቡዕ እለት ገፁ ላይ ባሰፈረው ፅሁፍ ፌስቡክ ለሦስት ወራት "ከህብረተሰብ አካላትና ምሁራን" ጋር ምክክር ካደረገ በኋላ የነጮችን ብሔርተኝነት ከነጮች የበላይነትና ከሌሎች የተደራጁ የጥላቻ ቡድኖች "መለየት" አይቻልም ብሏል።
በኒውዚላንድ የተደረገውን ጥቃት ተከትሎ ብዙ መሪዎች የማህበራዊ ሚዲያዎች በገፆቻቸው ላይ ለሚለጠፏቸው ፅንፈኛ ይዘቶችን ሃላፊነት እንዲወስዱ አስጠንቅቀዋል።
የኒውዚላንዷ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደርን ስለማህበራዊ ሚዲያዎች ስትናገር "መልዕክቱን የለቀቀው ሰው ብቻ ሳይሆን አሳታሚዎቹም" እንደዚህ አይነት ይዘቶች ሲለቀቁ ሃላፊነት አለባቸው ብለዋል።
50 ሰዎችን የገደለው የኒውዚላንዱ ጥቃት ምስል ከማህበራዊ መድረኩ ላይ ከመውረዱ በፊት ከ4 ሺህ ጊዜ በላይ እንደታየ ፌስቡክ አስታውቋል።
ድርጅቱ በ24 ሰዓት ውስጥ የምስሉ 1.2 ሚሊዮን ቅጂዎችን ከመለቀቅ የከለከለ ሲሆን 300 ሺህ የሚሆኑትን ደግሞ ከድረ ገፁ ላይ አጥፍቷል።
የፈረንሳይ ሙስሊሞችን የሚወክል አንድ ቡድን ፌስቡክና ዩትዩብ ምስሉን በገፃቸው ስላስተላለፉ ከሷቸዋል
Share:

በአፍርካ 10 ምርጥ አየር መንገድ

በአፍርካ ውስጥ ከሚገኙት አየር መንገዶች 10 ምርጥ አየር መንገዶች

በአየር መጓጓዣ የአቪዬሽን ኤጀንሲ ዋና ዋና ምህንድስና እድገትና የአፍሪካ አየር መንገዶች የቱሪስቶች እና ነጋዴዎች, የግል አየር መጓጓዣዎች እና ሌሎችም አህጉራትን ለማጓጓዝ የተተወ ነው. አየርን ማሽከርከር የ 24 ሰዓት ሥራ ነው እናም ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት አስፈላጊ ነው. በችግሮች, በቅንጦት እና በችግሮች ሰዓት ትክክለኛውን ቦታ, አመራር, ተነሳሽነት እና ሰዓት ይጠይቃል. እንደ Skytrax ዘገባ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ አምስት ኮከብ ያላቸው አምስት አየር መንገዶች ብቻ ናቸው.

ምንም እንኳን የአፍሪካ አቪዬሽን ኢንዱስትሪ ጥራት ባላቸው ጥራት ደረጃዎች, በዕድሜ የገፉ አውሮፕላኖች እና ሌሎች ችግሮች አሉበት. እንደዚያም ሆኖ አንዳንድ የአፍሪካ አየር መንገዶች ለተሳፋሪዎች ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት ችለዋል. የአፍሪካ 10 ምርጥ አየር መንገዶች ዝርዝር ከዚህ በታች ቀርቧል:

1 የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማውን ሙሉ በሙሉ በመንግስት ባለቤትነት የተያዘው እና በታህሳስ 1945 እ.ኤ.አ. የተጀመረ ሲሆን ወደ ዓለም ዓቀፍ በረራዎች በ 1951 ተቀላቀለ ።
የቦሌ ኦፕሬሽን ማእከል እና ዋና መሥሪያ ቤት በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የው።
ኢትዮጵያ ከሌሎች የአየር ማጓጓዣ አውሮፕላኖች ይልቅ በአፍሪካ ተጨማሪ መዳረሻዎችን ይጥላል. በኢንዱስትሪ ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኩባንያዎች አንዱ ነው. በአፍሪካ ውስጥ በጣም ገቢ ከሚያስመዘገቡ አየር መንገዶች መካከል አንዱ ነው.

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እ.ኤ.አ. ከዲሴምበር 2011 ጀምሮ የ Star alliance አባል ኩባንያ አባል ሲሆን 42 passenger እና 6 freighter  አውሮፕላኖች አገልግሎት ሲሰጥ ለ 62 አገራት እና 17 የሀገር ውስጥ መዳረሻዎች አገልግሎት ይሰጣል.
በተጨማሪም የ 50.4 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቢያ አፈፃፀም ሪፖርት አወጣ. አየር መንገድ በአምስት ደረጃ ኮከብ በ Skytrax ደረጃ መስፈርት አለው

2 የደቡብ አፍ አየር መንገድ


በደቡብ አፍሪካ ትልቁ የሆነው አየር መንገድ South African Airways በኦቲ ትምቦ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ  ውስጥ ዋና መሥሪያ ቤት አለው. አየር መንገዱ ከአለም አቀፍ አውሮፕላኖች (ስዊድን ኤክስፕር), ሳ ኤ አይ አርቢንግ እና ዝቅተኛው አውሮፕላን ማሽን, ማንጎ, በደቡብ አፍሪካ እና በአህጉሪቱ በሙሉ እንዲሁም ከጂሃም አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከጆሃንስበርግ 5 አከባቢዎች ጋር በመተባበር በዓለም ዙሪያ ወደ 56 መዳረሻዎች ይጓዛል. 54 አውሮፕላኖች ሙሳ ዙዋን እ.ኤ.አ. ከኖቨምበር 2015 ጀምሮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኖ ሲሰራ ቆይቷል. እስከ 2016 ድረስ 8 525 ሰራተኞች አሉት.

3 አየር ማይሪሸስ


አውሮፕላን ማይሪክ አቪዬሽን አየር መንገድ ሞሪሸስ የተባለው አየር መንገድ አውሮፕላን ማረፊያ ነው. አየር መንገዱ ዋና መሥሪያ ቤቱ በታተሪው ሉዊስ ሞሪሺየስ የሚገኘው አየር ሞሪሸስ ሴንተር ነው. ዋናው ማዕከል ሰር ሰርዌሳጋር ራምሆልም ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ነው. ኩባንያው ከሰሃራ በታች አፍሪካ በአራተኛው አውሮፕላን ማረፊያ ሲሆን በአውሮፓ, በአፍሪካ እና በሕንድ ውቅያኖስ ገበያዎች ውስጥ ከፍተኛ ቦታ አለው.

አውሮፕላን ማይሪክስ በአውሮፓውያን, በአፍሪካ እና በሕንድ ውቅያኖስ ገበያ ውስጥ ትልቅ ቦታ ነበራት. በአፍሪካ ደቡባዊ ምሥራቅ ጠረፍ አቅራቢያ በአሜሪካ ውቅያኖስ ላይ አውሮፕላን ማረፊያ አየር መንገዱ በአየር ሞሪሸስ ሴንትራል ፖርት ሉዊስ ሞሪሺየስ ይገኛል.

አየር ማይሪሸስ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት በጣም አስተማማኝ የአየር መንገዶች አንዱ ሆኗል. ይህ አውሮፕላን ማረፊያ በአውሮፕላን ደህንነት አውታረ መረብ የተረጋገጠ ሲሆን አየር መንገዱ ምንም ዓይነት አደጋ አጋጥሞት አያወቅም።

4 አየር ሲሸልስ

አየር ሲሸልስ / Seychelles / በሴይሌ ደሴት የሲሸልስ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋና መስሪያ ቤት ነው. ቻርተር አገልግሎቶች እና አለም አቀፍ በረራዎች ያካሂዳል. ዋናው መስራቤቱ ሲሸልስ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ነው. በሲሸልስ ውስጥ በቱሪዝም የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ምሰሶዎች ዋነኛው ነው. አየር መንገዱ አቡዳቢ, አንታናናሪቮ, ዮሃንስበርግ, ሞሪሺየስ, ሙምባይ, ዱባይ, ዱስሰንዲፍ እና ፓሪስ ላይ አለም አቀፍ በረራዎችን ያቀርባል.

5 ኬንያ አየር መንገድ

የኬንያ አየር መንገድ ኢንሹራንስ ኩባንያ, በኬንያ ኤ. ኩባንያው የምሥራቅ አፍሪካን አውሮፕላን ከተስፈፈ በኋላ በ 1977 ተቋቁሟል. ዋናው ጽ / ቤት የሚገኘው ናይሮቢ ውስጥ በጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ ውስጥ ነው. ኤርፖርቱ ሙሉ በሙሉ በኬንያ መንግሥት እስከ ኤፕሪል 1995 ድረስ ሙሉ በሙሉ በባለቤትነት የተያዘ ነበር. በ 1996 ዓ.ም. ስለዚህ. በአሁኑ ጊዜ የኬንያ አየር መንገድ የግል ሽርክና ነው. የኬንያ መንግሥት 29.8%, የ KLM 26.73% ኩባንያ አለው. የተቀሩት ማጋራቶች በግል ባለቤቶች የተያዙ ናቸው. አክሲዮኖች በናይሮቢ ስቶክየስተር, በዲሬይ ሰላማዊ ልውውጥ እና በኡጋንዳ የሲኤምኢሲንግ ትሬድ ላይ ይገበያሉ. እ.ኤ.አ. ጥር 2013 ኬንያ አየር መንገድ ከሚሰሩ ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት አንዷ ነች ተብላለች. ከአፍሪካ 10 የአውሮፓውያን አየር መንገዶች ከአፍሪካ ደቡብ አፍ አየር መንገድ, ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከግብጽ አየር ማእከል ጋር ተያይዞ. አየር መንገዱ እ.ኤ.አ. በሰኔ 2010 ውስጥ SkyTeam ሙሉ አባል ሆነ እና ከ 1977 ጀምሮ የአፍሪካውያን አየር መንገድ ማህበር አባል ነው

6 ንጉሳዊ አየር መንገድ/ሞሮኮ/

ሬድ በመባል የሚታወቀው ሮያል አየር ኤሮክ የሞሮካን ብሔራዊ የጋርዮሽ እና የሃገሪቱ ትልቁ የአየር መንገድ ነው. ሬድበሞሮኮ መንግስት ሙሉ በሙሉ የተያዘ ሲሆን በዋና ከተማው በካስቡላካ-አናፍ አየር ማረፊያ አለው. አውሮፕላን ማረፊያ በሞምዲ አውሮፕላን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በመሥራት በአፍሪካ, በእስያ, በአውሮፓ እና በሰሜን እና በደቡብ አሜሪካ በአለም አቀፍ በረራዎች ላይ አልፎ አልፎ ቻርተር በረራዎች

7 ታጋ አንጎላ አየር መንገድ

ታጋ አንጎላ አየር መንገድ E.P. (ፖርቱጋልኛ-ታካግ ሊዊንስ አሬሳ ዴ አንጐላ ፖ.ፒ.) በመንግስት ባለቤትነት የተያዘው የአንጎላ አየር መንገድ ነው. በሉዋንዳ የተመሰረተው አየር መንገዱ በአንጎላ, በአፍሪካ በሚገኙ የመጓጓዣ አገልግሎቶች እና በብራዚል, በኩባ, በቻይና እና ፖርቱጋል በአውሮፓ ውስጥ በአገር ውስጥ አገሌግልቶችን ያንቀሳቅሰዋል. አየር መንገዱ መጀመሪያ የተገነባው በ 1938 ዓ.ም ነው።
አሁን የዓለም አየር ትራንስፖርት ማህበር እና የአፍሪካ አየር መንገድ አባል ነው.

8 Fastjet

Fastjet Plc (LSE: FJET) በብሪታንያ የተመሠረተው የቡድን ኩባንያ ነው. የኩባንያው ዓላማ የአፍሪካን አየር መንገድ የመጀመሪያውን ዝቅተኛ ዋጋ ያለው, የፓን አፍሪካን አየር መንገድን ለመገንባት ነው. በቬንዚኒያ ውስጥ እ.ኤ.አ. በኖቬምበር 2012 ውስጥ በፋይዝ ራይትስ ዎች ውስጥ የሚደረጉ በረራዎች ተካሂዷል. በአካባቢያዊ ባለቤትነት እና ሌሎች መስፈርቶች ለማሟላት አሁን ያለው ስትራቴጂ በአገር ውስጥ ተዘዋዋሪ አየር መንገድን በመፍጠር አገልግሎቶችን ለማንቀሳቀስ የጋራ ስም አሰጣጥ, የስራ አፈፃፀም ደረጃዎች እና የሽያጭ መድረኮችን መፍጠር ነው. እንደ Fastjet Tanzania እና Fastjet Zimbabwe የሚባሉት አየር መንገዶች በኦክቶበር 2015 ጀምሯል. ምንም እንኳን Fastjet ዛምቢያ በጣም የተራቀቀ የእቅድ ዝግጅት ደረጃ ላይ ቢገኝም, እ.ኤ.አ. 2016 ግን ቢያንስ እስከ 2016 የመጨረሻ ሩብ ድረስ መዘግየቱ እየተዘዋወረ እንደነበረ ታውቋል.

9 ኩሉላ

kulula.com, አንዳንድ ጊዜ በቀላሉ በ kulula (የሉሉኛ ቋንቋዎች የሉሉ እና የሶሳ ቋንቋዎች ማለት ቀላል ነው) ማለት የደቡብ አፍሪካ አሮጌ አየር መንገድ አየር መንገድ ነው, ከኦቲ ትሞ ኤ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ እና ላንስሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋና ዋናዎቹ የአገር ውስጥ መንገዶች ከጆሃንስበርግ ወጣ. የአየር መንገዱ ዋና መሥሪያ ቤት በቦናአን ፓርክ, ኪምሶን ፓርክ, ኤትኩርሁኒ, ጋውቴን ውስጥ ይገኛል.

10 ማንጎ

ማንጎ አየር መንገድ አክሲዮን ማህበር ማንጎን ይጠቀማል, መንግስታዊ ያልሆነ የደቡብ አፍሪካ የአነስተኛ የአየር መንገድ ነው, በጆሃንስበርግ ኦሮተሞቦ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እና በደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ ቅርንጫፍ.
Share:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አደጋ ከኢንዶኔዢያው ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው ተነገረ

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የተገኘው 
 መረጃ አደጋው ባለፈው ጥቅምት ወር በኢንዶኔዢያ ባሕር ላይ ከተከሰከሰው አውሮፕላን ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው እንደሚያመለክት የኢትዮጵያ ትራንስፖርት ሚኒስትር ገለጹ።
 ከኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የተገኘው    መረጃ አደጋው ባለፈው ጥቅምት ወር በኢንዶኔዢያ ባሕር ላይ ከተከሰከሰው አውሮፕላን ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው እንደሚያመለክት የኢትዮጵያ ትራንስፖርት ሚኒስትር ገለጹ

አደጋው የገጠማቸው ሁለቱ አውሮፕላኖች ቦይንግ 737 ማክስ ኤይት የተባሉ ሲሆኑ በደረሰባቸው አሰቃቂ አደጋ በውስጣቸው የነበሩ የሁሉም ተጓዦች ህይወት አልፏል
ባለፈው ሳምንት ከአዲስ አበባ ከተነሳ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ አደጋ የደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ይዟቸው የነበሩት 157 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።
የአውሮፕላኑ የበረራ መመዝገቢያ ሳጥኖች ወደፈረንሳይ ባለፈው ሳምንት ተወስደው የነበረ ሲሆን፤ የትራንስፖርት ሚኒስትሯ የበረራ መረጃው ከአውሮፕላኑ የመረጃ ማስቀመጫ ክፍል ላይ በአግባቡ እንደተሰበሰበ ተናግረዋል።
ከአውሮፕላኑ የተገኘውና አደጋው ስለደረሰበት አውሮፕላን ለሚደረገው ምርመራ ጠቃሚ መረጃ ይሆናል የተባለው የበረራ መረጃ ምርመራውን ለሚያከናውነው ቡድን መሰጠቱም ተገልጿል።
ከተሰበሰበው መረጃም "በኢትዮጵያ እየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የደረሰው አደጋ ከወራት በፊት በኢንዶኔዢያው ተመሳሳይ አውሮፕላን ላይ ከደረሰው አደጋ ጋር ግልፅ መመሳሰል ታይቷል" ሲሉ ሚኒስትሯ ተናግረዋል።
የበረራ መመዝገቢያ መረጃ እንደሚያመለክቱት በሁለቱም የአውሮፕላን አደጋዎች ላይ ድንገተኛ የከፍታ መለዋወጥ እንደታየ፤ ይህም አውሮፕላኖቹ ያልተጠበቀ ከፍና ዝቅ የማለት ተመሳሳይ አጋጣሚዎች እንደተስተዋለባቸው ተገልጿል።
የኢትዮጵያ የምርመራ ባለሙያዎች በጥቂት ቀናት ውስጥ ወደሃገራቸው እንደሚመለሱና ተጨማሪ መረጃዎችን ማግኘት እንደሚቻል ጠቁመው፤ "የመጀመሪያ ደረጃ የምርመራው ውጤት በ30 ቀናት ውስጥ ይፋ ይሆናል" ብለዋል ሚኒስትሯ።
የቦይንግ ኩባንያ ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ዴኒስ ሙሊንበርግ እንደተናገሩት ድርጅታቸው በአውሮፕላን አደጋው ዙሪያ በሚደረጉ ምርመራዎች ላይ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል።
ከድርጅቱ በወጣው መግለጫ ላይ ሥራ አስፈጻሚው እንዳመለከቱት በአውሮፕላኑ ውስጥ ያለውን የበረራ መቆጣጠሪያ ሥርዓት የሚመራውን ሶፍትዌር ለማሻሻል እየሰራ እንደሆነም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን ምን ገጠመው?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ 302 መጋቢት 01 ቀን 2011 ዓ.ም ጠዋት ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ በመነሳት ናይሮቢ ለመድረስ ነበር ዕቅዱ።
አውሮፕላኑ ከተነሳ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ አብራሪው ችግር እንደገጠመው አመልክቶ ተመልሶ እንዲያርፍ ጠየቀ።
በአየር ሁኔታ ምክንያት ዕይታን የሚያስቸግር ነገር አልነበረም የሚለው የአየር ትራንስፖርት እንቅስቃሴን የሚከታተለው ፍላይትራዳር24 "አውሮፕላኑ ከተነሳ በኋላ ወደላይ የሚወጣበት ፍጥነት የተረጋጋ አልነበረም" ብሏል።
አደጋው በተከሰተበት ስፍራ ነበርኩ ያለ የዓይን እማኝ ለቢቢሲ እንደተናገረው አውሮፕላኑ መሬት ላይ ሲወድቅ ከባድ እሳት ተፈጥሮ ነበረ።
የፈረንሳይ የአየር ትራንስፖርት ደህንነት መርማሪዎች የአውሮፕላኑን የበረራ መረጃ መመዝገቢያንና የበረራ ክፍል የድምጽ መቅጃን በመመርመር ያገኙትን ምርመራውን ለሚያከናውኑት የኢትዮጵያ ባለሙያዎች አስረክበዋል።
በኢንዶኔዢያው አውሮፕላን ላይ ምን ተከሰተ?
ጥቅምት 19/2011 ዓ.ም የላየን ኤር በረራ 610 ከኢንዶኔዢያዋ መዲና ጃካርታ ከተነሳ በኋላ በመከስከሱ የ189 ሰዎች ህይወት አልፏል።
በኋላ ላይ የአደጋ መርማሪዎች እንደደረሱበት አውሮፕላኑ ሽቅብ በጣም ከፍ ወዳለ አቅጣጫ እንዳይወጣ የሚቆጣጠረው የአውሮፕላኑ ሥርዓት ላይ ችግር እንደነበረበት አመልክተዋል።
በዚህም ሳቢያ በዚህ በረራ ወቅት የመቆጣጠሪያ ሥርዓቱ በተደጋጋሚ አውሮፕላኑን ወደታች እንዲያዘቀዝቅ ያደርገው ነበር ተብሏል።
የአውሮፕላኑ የመቆጣጠሪያ ሥርዓት ወደታች እንዲያዘቀዝቁ ከማድረጉ በፊት አብራሪዎቹ ይህንን ችግር የአውሮፕላኑን አፍንጫ ወደላይ ከፍ በማድረግ ለማስተካከል ጥረት አድርገዋል። ይህም በአውሮፕላኑ ላይ ከሃያ ጊዜ በላይ እንደተከሰተ ተገልጿል።
የኢንዶኔዢያው አውሮፕላን ከተከሰከሰ ከወራት በኋላ በተመሳሳይ ሁኔታ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የደረሰውን አደጋ ተከትሎ በዓለም ዙሪያ ያሉ አየር መንገዶች ያሏቸውን ቦይንግ ማክስ ኤይት አውሮፕላኖችን ከበረራ ውጪ አድርገዋል
Share:

ዕጣ የወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞን ቀሰቀሱ

የ20/80ና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ ይፋ ከመሆን ጋር ተያይዞ ቦታው የኦሮሚያ ነው በሚል በ10 ኦሮሚያ ክልል ከተሞች ተቃውሞዎች ተቀስቅሰዋል።

የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ የተገነቡባቸው አካባቢዎች በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ሆነው የአዲስ አበባ መስተዳድር ውሳኔ የሚያሳልፈው እንዴት ነው፤ ለተፈናቃዮቹ አርሶ አደሮች የተሰጠው ካሳ እዚህ ግባ የማይባል ነው፤ የተቀናጀው ማስተር ፕላን ቅጥያ ነው የሚሉ ሀሳቦችን ተቃዋሚዎቹ አንስተዋል.
በምስራቅ ኦሮሚያ ጪሮ ከተማ ቢቢሲ ያነጋገረው አንድ ሰልፈኛ " በዚህ ተቃውሞ ላይ ዋነኛ መልዕክታችን በአዲስ አበባ አካባቢ ያሉት መሬቶች ለኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ሊመለስ ይገባል" የሚል ነው። ተቃዋሚው ጨምሮም ለብዙዎች ሞት ምክንያት የሆነው አወዛጋቢው የተቀናጀ ማስተር ፕላን ሊመለስ አይገባም ብሏል።
ተቃውሞዎቹ በሻሸመኔ፣ ጪሮ፣ ጂማ፣ አሰላ፣ አዳማና ሂርና ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የተስፋፉ ሲሆን በሻሸመኔ አካባቢ የሚገኙ ሰልፈኞች "ኦዲፒ ያልነውን ረስታችሁታል፤ መሬታችን የደም ስራችን ነው" የሚሉ መፈክሮችን ይዘው ነበር።
በትናንትናው ዕለት 51 ሺህ 229 የጋራ መኖሪያ ቤቶች በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል የዕጣ ማውጫ ስነ ስርአት ለተጠቃሚዎች የተላለፈ ሲሆን፤ ከአካካቢው ለተነሱ አርሶ አደሮችና ልጆቻቸው ያለ እጣ እንዲሰጣቸው በከተማው አስተዳደር ካቢኔና በቤቶች አስተዳደር ውሳኔ መሰረት ያለ ዕጣ እንዲተላለፍ መወሰኑን ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ በትናንትናው ዕለት ገልፀዋል።
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ሲገነቡ የተጎዱ ሰዎች እንዳሉ ያልደበቁት ምክትል ከንቲባው "በተለይም የእርሻ መሬታቸውን ለነዚህ ተግባራት ሲሉ የለቀቁና ለኢኮኖሚና ማህበራዊ ቀውስ የተዳረጉ የአርሶ አደር ቤተሰቦችና ልጆቻቸው ህመማችሁ የእኛ መሆኑን እንድታውቁ" የሚል መልእክት አስተላልፈዋል።
ምክትል ከንቲባው ይህንን ቢሉም ኦሮሚያ ውስጥ ተቀስቅሶ ለረጅም ጊዜ ለዘለቀው ሕዝባዊ ተቃውሞ መነሻ ምክንያት እንደሆነ የሚነገርለትና ከ2006 ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ የነበረው የአዲስ አበባና በዙሪያዋ ያሉ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ ማስተር ፕላን ቅጥያ ነው የሚሉ ትችቶችም እየተሰሙ ነው።
ምንም እንኳን የተቀናጀው ማስተር ፕላን ከፍተኛ ተቃውሞዎችን ተከትሎ ውድቅ ቢደረግም የቀድሞው የአዲስ አበባ ከንቲባና ኦህዴድ ሊቀ መንበር አቶ ኩማ ደመቅሳ ጉዳዩ ከመፈናቀል ጋር አብሮ ስለመጣ እንጂ "ተራማጅ አስተሳሰብ ነው ብዬ አስባለሁ፤ ጊዜ ሊወስድ ይችላል እንጂ ማስተር ፕላኑ አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል" ብለው ለቢቢሲ መናገራቸው የሚታወስ ነው.
ምንም እንኳን ከመንግሥት በኩል ምንም አይነት መግለጫ ባይሰጥም በቅርቡ ከውጭ ሀገር የተመለሰው የተባበሩት ኦነግ በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ያለውን ድንበር መወሰን ያለበት የኦሮሚያ ክልል ነው የሚል ነው።
በ13ኛው ዙር የ20/80 ቤቶች 32ሺ 653 ቤቶችና በ2ኛ ዙር የ40/60 ቤቶች ለተጠቃሚዎች የሚተላለፉ ሲሆን፤ ከነዚህም ውስጥ 1ሺ 248 ስቱዲዮ፣ 18ሺ 823 ባለ አንድ መኝታ፣ 7ሺ 127 ባለሁለት መኝታ እና 5ሺ455 ደግሞ ባለ ሶስት መኝታ መሆናቸው ተገልጿል።
በ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውስጥ የሚካተቱትም በ1997 ተመዝግበው በ2005 ዓ.ም በነባር መደብ የተመዘገቡና በ2005 ዓ.ም የአዲስ ባለ ሶስት መኝታ ተመዝጋቢ ደንበኞች መሆኑ ተገልጿል።
Share:

በወንድሜ ለአምስት ዓመታት ተደፍሬአለሁ

መገናኛ አካባቢ የሚገኝ ፀጥ ያለ መንደር ነው። ሰባት ወይም ስምንት የሚሆኑ ልጅ ያቀፉ አፍላ ታዳጊዎች እየተሳሳቁ ከአንድ ትልቅ ግቢ በመውጣት ላይ ነበሩ። ሁሉም ልጅ የያዙና በእድሜም ለእናትነት ገና መምሰላቸው ትኩረት ይስባል። ምን እየተባባሉ እንደሆነ ለመስማትም ያጓጓል።
እነሱን አልፈን ወደ ውስጥ ዘለቅን።

የ23 ዓመት ወጣት ነች። ከገፅታዋ ምንም ነገር ማንበብ አይቻልም። ገፅታዋም ሆነ ሁለንተናዋ ፀጥ ያለ ነው። ከዓመታት በፊት ወደ እዚህ ግቢ ስትመጣ የሥራ ማመልከቻ ለማስገባት ወይም ሥራ ለመጀመር አልነበረም። ይልቁንም በእናቷ ልጅ በወንድሟ ተደፍራ ከደረሰባት ከባድ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ለማገገምና መጠለያ ለመሻት ነበር።
የደረሰባት ነገር ሰው እንድትፈራ አድርጓት ነበርና በሙሉ አይኗ ሰው ማየት ያስፈራት፤ ቃላት አውጥቶ መናገርም ይከብዳት እንደነበር ታስታውሳለች።
"ከባድና እጅግ አሳዛኝ ህይወት አሳልፌአለው" ትላለች ጊዜውን በማስታወስ። የጉዳቷ መጣን በህይወት እየኖርኩ ነው የማያስብል ቢሆንም ያን ቀን አልፋ ዛሬ ቀና ብላ መራመድ ችላለች። ዛሬ የምትፈልግበት መድረስና ህልሟን መኖር እንደምትችልም በእርግጠኝነት ትናገራለች።
ዛሬ ያኔ ተደፍራ የተጠለለችበትና ለተደፈሩ ሴቶች ድጋፍ የሚያደርገው 'የሴቶችና የህፃናት ማረፊያ' ውስጥ ለመሥራት ችላለች።
ምንም እንኳ ያን ጊዜ ማስታወስ ቢያማትም ያለፈችበት መንገድ ሴቶች ለፆታዊ ጥቃት እንዳይጋለጡ አስተማሪ ይሆናል የሚል ፅኑ እምነት ስላላት የሆነችውን ትናገራለች።
ሊያስተምራት አዲስ አበባ ያመጣት ትልቅ ወንድሟ ፖሊስ ነበር። ያኔ እሷ የ16 ዓመት ታዳጊ ነበረች። የሚኖሩት ወንድሟ በተከራየው ቤት ነበር።
"ልጅ ስለነበርኩ ብዙ ነገር አላውቅም፤ መናገርም አልችልም ነበር። ሰው ሳይ ተመሳሳይ ጥቃት ያደርሱብኛል ብዬ ፍራቻ ነበረብኝ" በማለት የነበረችበትን የሥነ ልቦና ስብራት ታስታውሳለች።
ሰው አይቷት ሚስጥሯን የሚያውቅ ይመስላት ስለነበር ትምህርት ቤት መሄድና መመለስ፤ ክፍል ውስጥ መቀመጥም እጅግ ስለከበዳት ትምህርት ቤት መሄድ አቆመች።
ወንድሟ ለአምስት ዓመታት አብረው ሲኖሩ ደፍሯታል። በዚህ ጊዜ ውስጥ ሦስት ጊዜም ፅንስ እንድታቋርጥም እንዳደረጋት ትገልፃለች።
ልጅነትና የሥነ ልቦና ቀውስ እንዲሁም የወንደሟ ማስፈራራት ለማንም ምንም ትንፍስ ሳትል እንድትቆይ አድርጓት ነበር። ይኖሩ ከነበሩበት ቤት ለቅቀው ሌላ የኪራይ ቤት የገቡበት አጋጣሚ ግን ጉዳቷን አውጥቶ ለመናገር እድል ሰጣት።
በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁኔታዋን ያስተዋሉት አዲሷ የቤት አከራያቸው አንድ ቀን "ለምንድነው ሰው የማትቀርቢው? ዘመዱ ነሽ ወይ?" ሲሉ ድንገት ጠየቋት።
ሁለቱም ጥያቄዎች ለእሷ እጅግ ከባድ ነበሩ። ከምትኖርበት ስቃይ መውጣት ትሻ ነበርና አለባብሶ እንደነገሩ መልስ መስጠት አልፈለገችም። በሌላ በኩል እውነቱን መናገርም መከራ ሆነባት።
እንደምንም ከራሷ ጋር ታግላ የሆነችውን ለአከራይዋ ተናገረች። በነገሩ በጣም የደነገጡት አከራይ ይዘዋት በአቅራቢያ ወደሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ለመሄድ ምንም አላመነቱም።
ከፖሊስ ጣቢያ በኋላ ነበር የተደፈሩ ሴቶችን ወደሚያስጠልለውና የሕግ አገልግሎት ድጋፍ ወደሚያደርገው የሴቶች ማረፊያ ልማት ማኅበር የተወሰደችው።
ነገሩ ወደ ሕግ ከሄደ በኋላ ጉዳዩን የሰሙ ቤተሰቦቿ 'እሱ እንዲህ አያደርግም፤ ልጅ ስለሆነች ነው እንዲህ ያለ ነገር የምታወራው' በማለት በፍፁም ሊያምኗት አልቻሉም። በተለይም ትልቅ እህቷ ካለማመን አልፋ የወንድማቸውን ስም ለማጥፋት 'ያልሆነውን ሆነ እያለሽ ነው' በሚል ብዙ ሞግታታለች ዝታባታለችም።
"ከእናቴ ውጪ ቤተሰብ ሁሉ እንደ ቆሻሻ ተፀየፈኝ" በማለት ተበዳይ ሆና እንዴት የበዳይ እዳ ተሸካሚ እንደተደረገች ትናገራለች።
በሌላ በኩል ፖሊስ ጣቢያ በሄደችበት ወቅት ያየችው አቀባበል እንደሷ ያሉ የተደፈሩ ሴቶች ይብስ ፈርተው እንዳይናገሩ የሚያደርግ እንደነበር ታስታውሳለች።
ሃዘኔታ በሌለው አንደበት 'ነይ እዚህ ጋር' 'እዛጋ' 'እስከዛሬ ምን ትሰሪ ነበር?' ተብላለች።
ይህ የእሷ ብቻ ሳይሆን የብዙ ሴቶች አስከፊ እጣ ነው። በማህበረሰቡ እንዲህ ስላደረግሽ ነው፣ እንደዛ ባታደርጊ ኖሮ በሚሉ የምክንያት ድርደራዎች ለመደፈራቸው ራሳቸው ጥፋተኛ ተደርገው አንገታቸውን እንዲደፉ የተደረጉ ሴቶችን ቤት ይቁጠራቸው።
በቀድሞ መጠለያዋ በዛሬው የሥራ ቦታዋ በወንድም፣ በአባት፣ በአያቶቻቸውም ጭምር የተደፈሩና የወለዱ ሴቶችም ጭምር አጋጥመዋታል። ሁሉም በቤተሰባቸውና በማኅበረሰባቸው ለመደፈራቸው ጥፋተኛ የተደረጉና የተወገዙ መሆናቸውን ትናገራለች።
"እኔ ስለ ሕግ ብዙ አላውቅም፤ ግን ካለፍኩበትና ካየሁት በሕግ በኩል ያለው ነገርም ደስ አይልም።"
በተለያዩ ምክንያቶች ደፋሪዎች ነፃ ሆነው የመሄድ እድል ያገኛሉ። በተመሳሳይ በእሷ ጉዳይም ክስ ተመስርቶ የነበረ ቢሆንም ክሱ የትም ሳይደርስ፤ ወንድሟም ሳይጠየቅ መቅረቱን ትናገራለች።
"ህመሜን ተቋቁሜ ችሎት ላይ ብቆምም መጨረሻው አላማረም። እዚህ ላይ ብዙ ማለት አልፈልግም" ትላለች።
ባደረገችው ተደጋጋሚ የፅንስ ማቋረጥ የማህፀን ጉዳት ደርሶባት ለረዥም ጊዜ ህክምና ስትከታተል ቆይታለች። በዚሁ ምክንያት ዛሬም ከባድ የወገብ ህመም ስላለባት ለቃለ መጠይቅ ባገኘናት ወቅትም በሃኪም የታዘዘ የወገብ መደገፊያ ቀበቶ አድርጋ ነበር።
ይህ ሁሉ ቢሆንም ግን "በጣም የተጎዳሁት በሥነ ልቦና ነው። በተለይም የቤተሰቦቼ ነገር በእጅጉ ጎድቶኛል ዛሬም አልወጣልኝም" ትላለች።
ወደ ማረፊያው ከገባች በኋላም ምግብ መብላት፣ ሰው እንዲቀርባትና እንዲያናግራትም አትፈልግም ነበር። ፍላጎቷ አንድና አንድ ነበር። ይቺን ዓለም ለመተው ራሷን ለማጥፋትም ሞክራ ነበር።
በመጨረሻ ከዚህ ያወጣት የተደረገላት የሥነ ልቦና ድጋፍ እንደሆነ ትናገራለች።
ደህና ሆና ወደ ራሷ ከተመለሰች በኋላ ደግሞ የተለያዩ የሙያ ስልጠናዎችን ወስዳለች። የሴቶች ማረፊያ ልማት ማኅበር ከሙያ ስልጠና በተጨማሪ ለተደፈሩ ሴቶች ራሳቸውን ከጥቃት መከላከል ይችሉ ዘንድ የቴኳንዶ ስልጠና የሚሰጥ ሲሆን እሷም ይህን ስልጠና ወስዳለች።
ሰዎች በጣም ሲጎዱ ብዙ ነገር አይፈልጉም። ምንም ነገር መስማትም መረዳትም ላይፈልጉ ይችላሉ። "ቢሆንም ግን ሰውን መርዳት የሚፈልጉ ብዙ ሰዎች ስላሉ መጀመሪያ እኛ ለመረዳትና ወደፊት ለመራመድ ፍቃደኛ መሆን አለብን" ትላለች።
ካጋጠማት አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጥቃትና ሰቆቃ ለመውጣትና ከባዱን ቀን ለማለፍ ብርታት ያገኘችው ከእራሷ ነበር። "ራሴን ማመኔ፣ የተበላሸ ህይወቴን ማስተካክል እንደምችል ማመኔ ረድቶኛል" ትላለች።
ባይናገሩም ከእሷ የበለጠ ከባድ ነገር ያሳለፉ ሴቶች ይኖራሉ ብላ ታስባለች። ማህበረሰቡ የእንደዚህ ያሉ ሴቶችን ታሪክ ሰምቶ መጠቋቆሚያ እያደረገ እንደገና ቁስላቸውን ባያደማ በታሪካቸው ብዙዎች እንዲማሩና የተሰበሩትም ቀና እንዲሉ ማድረግ ይቻል ነበር የሚል እምነት አላት።
"ሻርፕ ጠምጥመው ስብር ብለው የሚሄዱ ሴቶች ሳይ ሁሌም የእኔ ታሪክ ይመስለኛል" የምትለው ወጣቷ በእንደዚህ ያለ አጋጣሚ ለምታገኛቸው ሴቶች ምንም ባታደርግላቸው እንኳ ገፍታ እንደምታናግራቸውና እንደምትሰማቸው ትናገራለች።
ማኅበረሰቡ የሴቶች ጉዳይ ግድ እንደሚለው ከተማረና ካመነ በብዙ መልኩ እንደ እሷ የተደፈሩ ሴቶችን ሊያግዝ የሚችልበት መንገድ እንዳለ ታምናለች። ከሁሉም በላይ ደግሞ በዚህ ጥቃትን መከላከልም እንደሚቻል ይሰማታል።
ህፃናትም ይሁኑ ታዳጊዎች ያሉት ቤተሰብ በሉ፣ ጠጡ፣ ለበሱ እና ትምህርት ቤት ሄደው መጡ፤ ከሚለው ባሻገር ቤት ውስጥም ሆነ ውጪ ልጆቹ ላይ ጥቃት ሊፈፀም እንደሚችል ማወቅ አለበት። ይህም ልጆችን ለመጠበቅ ያስችላል ትላለች።
የቀድሞው ፆታዊ ጥቃት ተከላካይ ማኅበር የአሁኑ የሴቶች ማረፊያ ልማት ማህበር በደረሰባቸው ጥቃት የተጎዱ፣ የተሰበሩና 'ማን ይፈልገኛል?' ብለው ራሳቸውን ማጥፋት የፈለጉ በርካታ ሴቶችን ለመደገፍ ጥረት ያደርጋል። ለተደፈሩ ሴቶች የሕግ ድጋፍና የሙያ ስልጠና በመስጠት ከ15 ዓመታት በላይ አስቆጥሯል።
የድርጅቱ መስራች ወ/ሮ ማርያ ሙኒር ማን ይፈልገናል? በሚል ራሳቸውን ለማጥፋት ሞክረው የነበሩ ሴቶች ከፍተኛ ትምህርታቸውን ተከታትለው ህይወታቸው ተቀይሮ ማየት ለሳቸው ትልቅ ነገር እንደሆነ በየጊዜው ምሳሌ የሚሆኑ ሴቶችን ታሪክ ለሚያወጣው 'ተምሳሌት ገፅ' ተናግረዋል።
ማኅበሩ በአዲስ አበባ፣ በደሴና በሌሎች ቅርንጫፎቹ እያገለገሉ የሚገኙ ኢንጅነሪንግ፣ ማኔጅመንትና ሌላ ሌላም ያጠኑ ወጣት ሴቶችን አቅፏል። ታሪኳን የነገረችን ወጣትም አዲስ አበባ ውስጥ በሙያ አሰልጣኝነትና በሃላፊነት እያገለገለች ነው።
Share:
Women's Fashion Category

Popular Posts

Blog Archive

Recent in Sports

3/recentposts
[recent]

Tags

Recent Comments

Recent Post

LightBlog

Recent

Adbox

Popular

Recent Posts