• This is default featured slide 1 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 2 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 3 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 4 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 5 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

ፌስቡክ የነጭ ብሔረተኝነትናና የተገንጣይ አመለካከት አራማጆችን ሊያግድ ነው

ፌስቡክ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ "የነጮችን ብሔርተኝነትና መለየትን የሚያሞግሱና የሚደግፉ" ፅሁፎችን ከፌስቡክና ከኢንስተገራም ገፆች ላይ እንደሚያግድ አሳወቀ።
ትልቁ የማህበራዊ ሚዲያ ፌስቡክ የሽብርተኝነት ይዘት ያላቸውን ይዘቶች ከድህረገፁ ላይ ለመለየትና ለማስወገድ እንደሚሰራም ቃል ገብቷል።
ቁጣን የሚቀሰቅሱ አባባሎችን የሚፈልጉ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች እንደዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ወደ የሚከላከሉ የበጎ አድራጎት ገጾች በመምራት ድግፍ እንዲያገኙ ያደርጋል።
በኒውዚላንድ የሁለት መስኪዶች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶች በቀጥታ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከተላለፈ በኋላ የማህበራዊ ሚዲያዎች ጫና በዝቶባቸዋል።
ፌስቡክ ከዚህ በፊት የነጮችን ብሔርተኝነት የሚያሳዩ ይዘቶችን እንደ ዘረኝነት ስለማይቆጥራቸው በገፁ ላይ እንዲገኙ ፈቅዶ ነበር።
"የአሜሪካ አክራሪ የነጮች ቡድንና በስፔን ያለው የባስክ ተገጣይ ቡድኖች አስፈላጊ የሰዎች ማንነት ክፍል እንደመሆኑት ሁሉ" የነጭ ብሔርተኝነትም ተቀባይነት ያለው እንደሆነ ይቀበል ነበር።
ነገር ግን ረቡዕ እለት ገፁ ላይ ባሰፈረው ፅሁፍ ፌስቡክ ለሦስት ወራት "ከህብረተሰብ አካላትና ምሁራን" ጋር ምክክር ካደረገ በኋላ የነጮችን ብሔርተኝነት ከነጮች የበላይነትና ከሌሎች የተደራጁ የጥላቻ ቡድኖች "መለየት" አይቻልም ብሏል።
በኒውዚላንድ የተደረገውን ጥቃት ተከትሎ ብዙ መሪዎች የማህበራዊ ሚዲያዎች በገፆቻቸው ላይ ለሚለጠፏቸው ፅንፈኛ ይዘቶችን ሃላፊነት እንዲወስዱ አስጠንቅቀዋል።
የኒውዚላንዷ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደርን ስለማህበራዊ ሚዲያዎች ስትናገር "መልዕክቱን የለቀቀው ሰው ብቻ ሳይሆን አሳታሚዎቹም" እንደዚህ አይነት ይዘቶች ሲለቀቁ ሃላፊነት አለባቸው ብለዋል።
50 ሰዎችን የገደለው የኒውዚላንዱ ጥቃት ምስል ከማህበራዊ መድረኩ ላይ ከመውረዱ በፊት ከ4 ሺህ ጊዜ በላይ እንደታየ ፌስቡክ አስታውቋል።
ድርጅቱ በ24 ሰዓት ውስጥ የምስሉ 1.2 ሚሊዮን ቅጂዎችን ከመለቀቅ የከለከለ ሲሆን 300 ሺህ የሚሆኑትን ደግሞ ከድረ ገፁ ላይ አጥፍቷል።
የፈረንሳይ ሙስሊሞችን የሚወክል አንድ ቡድን ፌስቡክና ዩትዩብ ምስሉን በገፃቸው ስላስተላለፉ ከሷቸዋል
Share:

በአፍርካ 10 ምርጥ አየር መንገድ

በአፍርካ ውስጥ ከሚገኙት አየር መንገዶች 10 ምርጥ አየር መንገዶች

በአየር መጓጓዣ የአቪዬሽን ኤጀንሲ ዋና ዋና ምህንድስና እድገትና የአፍሪካ አየር መንገዶች የቱሪስቶች እና ነጋዴዎች, የግል አየር መጓጓዣዎች እና ሌሎችም አህጉራትን ለማጓጓዝ የተተወ ነው. አየርን ማሽከርከር የ 24 ሰዓት ሥራ ነው እናም ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት አስፈላጊ ነው. በችግሮች, በቅንጦት እና በችግሮች ሰዓት ትክክለኛውን ቦታ, አመራር, ተነሳሽነት እና ሰዓት ይጠይቃል. እንደ Skytrax ዘገባ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ አምስት ኮከብ ያላቸው አምስት አየር መንገዶች ብቻ ናቸው.

ምንም እንኳን የአፍሪካ አቪዬሽን ኢንዱስትሪ ጥራት ባላቸው ጥራት ደረጃዎች, በዕድሜ የገፉ አውሮፕላኖች እና ሌሎች ችግሮች አሉበት. እንደዚያም ሆኖ አንዳንድ የአፍሪካ አየር መንገዶች ለተሳፋሪዎች ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት ችለዋል. የአፍሪካ 10 ምርጥ አየር መንገዶች ዝርዝር ከዚህ በታች ቀርቧል:

1 የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማውን ሙሉ በሙሉ በመንግስት ባለቤትነት የተያዘው እና በታህሳስ 1945 እ.ኤ.አ. የተጀመረ ሲሆን ወደ ዓለም ዓቀፍ በረራዎች በ 1951 ተቀላቀለ ።
የቦሌ ኦፕሬሽን ማእከል እና ዋና መሥሪያ ቤት በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የው።
ኢትዮጵያ ከሌሎች የአየር ማጓጓዣ አውሮፕላኖች ይልቅ በአፍሪካ ተጨማሪ መዳረሻዎችን ይጥላል. በኢንዱስትሪ ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኩባንያዎች አንዱ ነው. በአፍሪካ ውስጥ በጣም ገቢ ከሚያስመዘገቡ አየር መንገዶች መካከል አንዱ ነው.

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እ.ኤ.አ. ከዲሴምበር 2011 ጀምሮ የ Star alliance አባል ኩባንያ አባል ሲሆን 42 passenger እና 6 freighter  አውሮፕላኖች አገልግሎት ሲሰጥ ለ 62 አገራት እና 17 የሀገር ውስጥ መዳረሻዎች አገልግሎት ይሰጣል.
በተጨማሪም የ 50.4 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቢያ አፈፃፀም ሪፖርት አወጣ. አየር መንገድ በአምስት ደረጃ ኮከብ በ Skytrax ደረጃ መስፈርት አለው

2 የደቡብ አፍ አየር መንገድ


በደቡብ አፍሪካ ትልቁ የሆነው አየር መንገድ South African Airways በኦቲ ትምቦ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ  ውስጥ ዋና መሥሪያ ቤት አለው. አየር መንገዱ ከአለም አቀፍ አውሮፕላኖች (ስዊድን ኤክስፕር), ሳ ኤ አይ አርቢንግ እና ዝቅተኛው አውሮፕላን ማሽን, ማንጎ, በደቡብ አፍሪካ እና በአህጉሪቱ በሙሉ እንዲሁም ከጂሃም አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከጆሃንስበርግ 5 አከባቢዎች ጋር በመተባበር በዓለም ዙሪያ ወደ 56 መዳረሻዎች ይጓዛል. 54 አውሮፕላኖች ሙሳ ዙዋን እ.ኤ.አ. ከኖቨምበር 2015 ጀምሮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኖ ሲሰራ ቆይቷል. እስከ 2016 ድረስ 8 525 ሰራተኞች አሉት.

3 አየር ማይሪሸስ


አውሮፕላን ማይሪክ አቪዬሽን አየር መንገድ ሞሪሸስ የተባለው አየር መንገድ አውሮፕላን ማረፊያ ነው. አየር መንገዱ ዋና መሥሪያ ቤቱ በታተሪው ሉዊስ ሞሪሺየስ የሚገኘው አየር ሞሪሸስ ሴንተር ነው. ዋናው ማዕከል ሰር ሰርዌሳጋር ራምሆልም ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ነው. ኩባንያው ከሰሃራ በታች አፍሪካ በአራተኛው አውሮፕላን ማረፊያ ሲሆን በአውሮፓ, በአፍሪካ እና በሕንድ ውቅያኖስ ገበያዎች ውስጥ ከፍተኛ ቦታ አለው.

አውሮፕላን ማይሪክስ በአውሮፓውያን, በአፍሪካ እና በሕንድ ውቅያኖስ ገበያ ውስጥ ትልቅ ቦታ ነበራት. በአፍሪካ ደቡባዊ ምሥራቅ ጠረፍ አቅራቢያ በአሜሪካ ውቅያኖስ ላይ አውሮፕላን ማረፊያ አየር መንገዱ በአየር ሞሪሸስ ሴንትራል ፖርት ሉዊስ ሞሪሺየስ ይገኛል.

አየር ማይሪሸስ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት በጣም አስተማማኝ የአየር መንገዶች አንዱ ሆኗል. ይህ አውሮፕላን ማረፊያ በአውሮፕላን ደህንነት አውታረ መረብ የተረጋገጠ ሲሆን አየር መንገዱ ምንም ዓይነት አደጋ አጋጥሞት አያወቅም።

4 አየር ሲሸልስ

አየር ሲሸልስ / Seychelles / በሴይሌ ደሴት የሲሸልስ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋና መስሪያ ቤት ነው. ቻርተር አገልግሎቶች እና አለም አቀፍ በረራዎች ያካሂዳል. ዋናው መስራቤቱ ሲሸልስ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ነው. በሲሸልስ ውስጥ በቱሪዝም የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ምሰሶዎች ዋነኛው ነው. አየር መንገዱ አቡዳቢ, አንታናናሪቮ, ዮሃንስበርግ, ሞሪሺየስ, ሙምባይ, ዱባይ, ዱስሰንዲፍ እና ፓሪስ ላይ አለም አቀፍ በረራዎችን ያቀርባል.

5 ኬንያ አየር መንገድ

የኬንያ አየር መንገድ ኢንሹራንስ ኩባንያ, በኬንያ ኤ. ኩባንያው የምሥራቅ አፍሪካን አውሮፕላን ከተስፈፈ በኋላ በ 1977 ተቋቁሟል. ዋናው ጽ / ቤት የሚገኘው ናይሮቢ ውስጥ በጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ ውስጥ ነው. ኤርፖርቱ ሙሉ በሙሉ በኬንያ መንግሥት እስከ ኤፕሪል 1995 ድረስ ሙሉ በሙሉ በባለቤትነት የተያዘ ነበር. በ 1996 ዓ.ም. ስለዚህ. በአሁኑ ጊዜ የኬንያ አየር መንገድ የግል ሽርክና ነው. የኬንያ መንግሥት 29.8%, የ KLM 26.73% ኩባንያ አለው. የተቀሩት ማጋራቶች በግል ባለቤቶች የተያዙ ናቸው. አክሲዮኖች በናይሮቢ ስቶክየስተር, በዲሬይ ሰላማዊ ልውውጥ እና በኡጋንዳ የሲኤምኢሲንግ ትሬድ ላይ ይገበያሉ. እ.ኤ.አ. ጥር 2013 ኬንያ አየር መንገድ ከሚሰሩ ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት አንዷ ነች ተብላለች. ከአፍሪካ 10 የአውሮፓውያን አየር መንገዶች ከአፍሪካ ደቡብ አፍ አየር መንገድ, ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከግብጽ አየር ማእከል ጋር ተያይዞ. አየር መንገዱ እ.ኤ.አ. በሰኔ 2010 ውስጥ SkyTeam ሙሉ አባል ሆነ እና ከ 1977 ጀምሮ የአፍሪካውያን አየር መንገድ ማህበር አባል ነው

6 ንጉሳዊ አየር መንገድ/ሞሮኮ/

ሬድ በመባል የሚታወቀው ሮያል አየር ኤሮክ የሞሮካን ብሔራዊ የጋርዮሽ እና የሃገሪቱ ትልቁ የአየር መንገድ ነው. ሬድበሞሮኮ መንግስት ሙሉ በሙሉ የተያዘ ሲሆን በዋና ከተማው በካስቡላካ-አናፍ አየር ማረፊያ አለው. አውሮፕላን ማረፊያ በሞምዲ አውሮፕላን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ አውሮፕላን ማረፊያዎችን በመሥራት በአፍሪካ, በእስያ, በአውሮፓ እና በሰሜን እና በደቡብ አሜሪካ በአለም አቀፍ በረራዎች ላይ አልፎ አልፎ ቻርተር በረራዎች

7 ታጋ አንጎላ አየር መንገድ

ታጋ አንጎላ አየር መንገድ E.P. (ፖርቱጋልኛ-ታካግ ሊዊንስ አሬሳ ዴ አንጐላ ፖ.ፒ.) በመንግስት ባለቤትነት የተያዘው የአንጎላ አየር መንገድ ነው. በሉዋንዳ የተመሰረተው አየር መንገዱ በአንጎላ, በአፍሪካ በሚገኙ የመጓጓዣ አገልግሎቶች እና በብራዚል, በኩባ, በቻይና እና ፖርቱጋል በአውሮፓ ውስጥ በአገር ውስጥ አገሌግልቶችን ያንቀሳቅሰዋል. አየር መንገዱ መጀመሪያ የተገነባው በ 1938 ዓ.ም ነው።
አሁን የዓለም አየር ትራንስፖርት ማህበር እና የአፍሪካ አየር መንገድ አባል ነው.

8 Fastjet

Fastjet Plc (LSE: FJET) በብሪታንያ የተመሠረተው የቡድን ኩባንያ ነው. የኩባንያው ዓላማ የአፍሪካን አየር መንገድ የመጀመሪያውን ዝቅተኛ ዋጋ ያለው, የፓን አፍሪካን አየር መንገድን ለመገንባት ነው. በቬንዚኒያ ውስጥ እ.ኤ.አ. በኖቬምበር 2012 ውስጥ በፋይዝ ራይትስ ዎች ውስጥ የሚደረጉ በረራዎች ተካሂዷል. በአካባቢያዊ ባለቤትነት እና ሌሎች መስፈርቶች ለማሟላት አሁን ያለው ስትራቴጂ በአገር ውስጥ ተዘዋዋሪ አየር መንገድን በመፍጠር አገልግሎቶችን ለማንቀሳቀስ የጋራ ስም አሰጣጥ, የስራ አፈፃፀም ደረጃዎች እና የሽያጭ መድረኮችን መፍጠር ነው. እንደ Fastjet Tanzania እና Fastjet Zimbabwe የሚባሉት አየር መንገዶች በኦክቶበር 2015 ጀምሯል. ምንም እንኳን Fastjet ዛምቢያ በጣም የተራቀቀ የእቅድ ዝግጅት ደረጃ ላይ ቢገኝም, እ.ኤ.አ. 2016 ግን ቢያንስ እስከ 2016 የመጨረሻ ሩብ ድረስ መዘግየቱ እየተዘዋወረ እንደነበረ ታውቋል.

9 ኩሉላ

kulula.com, አንዳንድ ጊዜ በቀላሉ በ kulula (የሉሉኛ ቋንቋዎች የሉሉ እና የሶሳ ቋንቋዎች ማለት ቀላል ነው) ማለት የደቡብ አፍሪካ አሮጌ አየር መንገድ አየር መንገድ ነው, ከኦቲ ትሞ ኤ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ እና ላንስሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋና ዋናዎቹ የአገር ውስጥ መንገዶች ከጆሃንስበርግ ወጣ. የአየር መንገዱ ዋና መሥሪያ ቤት በቦናአን ፓርክ, ኪምሶን ፓርክ, ኤትኩርሁኒ, ጋውቴን ውስጥ ይገኛል.

10 ማንጎ

ማንጎ አየር መንገድ አክሲዮን ማህበር ማንጎን ይጠቀማል, መንግስታዊ ያልሆነ የደቡብ አፍሪካ የአነስተኛ የአየር መንገድ ነው, በጆሃንስበርግ ኦሮተሞቦ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እና በደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ ቅርንጫፍ.
Share:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አደጋ ከኢንዶኔዢያው ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው ተነገረ

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የተገኘው 
 መረጃ አደጋው ባለፈው ጥቅምት ወር በኢንዶኔዢያ ባሕር ላይ ከተከሰከሰው አውሮፕላን ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው እንደሚያመለክት የኢትዮጵያ ትራንስፖርት ሚኒስትር ገለጹ።
 ከኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የተገኘው    መረጃ አደጋው ባለፈው ጥቅምት ወር በኢንዶኔዢያ ባሕር ላይ ከተከሰከሰው አውሮፕላን ጋር ተመሳሳይነት እንዳለው እንደሚያመለክት የኢትዮጵያ ትራንስፖርት ሚኒስትር ገለጹ

አደጋው የገጠማቸው ሁለቱ አውሮፕላኖች ቦይንግ 737 ማክስ ኤይት የተባሉ ሲሆኑ በደረሰባቸው አሰቃቂ አደጋ በውስጣቸው የነበሩ የሁሉም ተጓዦች ህይወት አልፏል
ባለፈው ሳምንት ከአዲስ አበባ ከተነሳ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ አደጋ የደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ይዟቸው የነበሩት 157 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።
የአውሮፕላኑ የበረራ መመዝገቢያ ሳጥኖች ወደፈረንሳይ ባለፈው ሳምንት ተወስደው የነበረ ሲሆን፤ የትራንስፖርት ሚኒስትሯ የበረራ መረጃው ከአውሮፕላኑ የመረጃ ማስቀመጫ ክፍል ላይ በአግባቡ እንደተሰበሰበ ተናግረዋል።
ከአውሮፕላኑ የተገኘውና አደጋው ስለደረሰበት አውሮፕላን ለሚደረገው ምርመራ ጠቃሚ መረጃ ይሆናል የተባለው የበረራ መረጃ ምርመራውን ለሚያከናውነው ቡድን መሰጠቱም ተገልጿል።
ከተሰበሰበው መረጃም "በኢትዮጵያ እየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የደረሰው አደጋ ከወራት በፊት በኢንዶኔዢያው ተመሳሳይ አውሮፕላን ላይ ከደረሰው አደጋ ጋር ግልፅ መመሳሰል ታይቷል" ሲሉ ሚኒስትሯ ተናግረዋል።
የበረራ መመዝገቢያ መረጃ እንደሚያመለክቱት በሁለቱም የአውሮፕላን አደጋዎች ላይ ድንገተኛ የከፍታ መለዋወጥ እንደታየ፤ ይህም አውሮፕላኖቹ ያልተጠበቀ ከፍና ዝቅ የማለት ተመሳሳይ አጋጣሚዎች እንደተስተዋለባቸው ተገልጿል።
የኢትዮጵያ የምርመራ ባለሙያዎች በጥቂት ቀናት ውስጥ ወደሃገራቸው እንደሚመለሱና ተጨማሪ መረጃዎችን ማግኘት እንደሚቻል ጠቁመው፤ "የመጀመሪያ ደረጃ የምርመራው ውጤት በ30 ቀናት ውስጥ ይፋ ይሆናል" ብለዋል ሚኒስትሯ።
የቦይንግ ኩባንያ ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ዴኒስ ሙሊንበርግ እንደተናገሩት ድርጅታቸው በአውሮፕላን አደጋው ዙሪያ በሚደረጉ ምርመራዎች ላይ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል።
ከድርጅቱ በወጣው መግለጫ ላይ ሥራ አስፈጻሚው እንዳመለከቱት በአውሮፕላኑ ውስጥ ያለውን የበረራ መቆጣጠሪያ ሥርዓት የሚመራውን ሶፍትዌር ለማሻሻል እየሰራ እንደሆነም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን ምን ገጠመው?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ 302 መጋቢት 01 ቀን 2011 ዓ.ም ጠዋት ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ በመነሳት ናይሮቢ ለመድረስ ነበር ዕቅዱ።
አውሮፕላኑ ከተነሳ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ አብራሪው ችግር እንደገጠመው አመልክቶ ተመልሶ እንዲያርፍ ጠየቀ።
በአየር ሁኔታ ምክንያት ዕይታን የሚያስቸግር ነገር አልነበረም የሚለው የአየር ትራንስፖርት እንቅስቃሴን የሚከታተለው ፍላይትራዳር24 "አውሮፕላኑ ከተነሳ በኋላ ወደላይ የሚወጣበት ፍጥነት የተረጋጋ አልነበረም" ብሏል።
አደጋው በተከሰተበት ስፍራ ነበርኩ ያለ የዓይን እማኝ ለቢቢሲ እንደተናገረው አውሮፕላኑ መሬት ላይ ሲወድቅ ከባድ እሳት ተፈጥሮ ነበረ።
የፈረንሳይ የአየር ትራንስፖርት ደህንነት መርማሪዎች የአውሮፕላኑን የበረራ መረጃ መመዝገቢያንና የበረራ ክፍል የድምጽ መቅጃን በመመርመር ያገኙትን ምርመራውን ለሚያከናውኑት የኢትዮጵያ ባለሙያዎች አስረክበዋል።
በኢንዶኔዢያው አውሮፕላን ላይ ምን ተከሰተ?
ጥቅምት 19/2011 ዓ.ም የላየን ኤር በረራ 610 ከኢንዶኔዢያዋ መዲና ጃካርታ ከተነሳ በኋላ በመከስከሱ የ189 ሰዎች ህይወት አልፏል።
በኋላ ላይ የአደጋ መርማሪዎች እንደደረሱበት አውሮፕላኑ ሽቅብ በጣም ከፍ ወዳለ አቅጣጫ እንዳይወጣ የሚቆጣጠረው የአውሮፕላኑ ሥርዓት ላይ ችግር እንደነበረበት አመልክተዋል።
በዚህም ሳቢያ በዚህ በረራ ወቅት የመቆጣጠሪያ ሥርዓቱ በተደጋጋሚ አውሮፕላኑን ወደታች እንዲያዘቀዝቅ ያደርገው ነበር ተብሏል።
የአውሮፕላኑ የመቆጣጠሪያ ሥርዓት ወደታች እንዲያዘቀዝቁ ከማድረጉ በፊት አብራሪዎቹ ይህንን ችግር የአውሮፕላኑን አፍንጫ ወደላይ ከፍ በማድረግ ለማስተካከል ጥረት አድርገዋል። ይህም በአውሮፕላኑ ላይ ከሃያ ጊዜ በላይ እንደተከሰተ ተገልጿል።
የኢንዶኔዢያው አውሮፕላን ከተከሰከሰ ከወራት በኋላ በተመሳሳይ ሁኔታ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የደረሰውን አደጋ ተከትሎ በዓለም ዙሪያ ያሉ አየር መንገዶች ያሏቸውን ቦይንግ ማክስ ኤይት አውሮፕላኖችን ከበረራ ውጪ አድርገዋል
Share:

ዕጣ የወጣባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞን ቀሰቀሱ

የ20/80ና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ ይፋ ከመሆን ጋር ተያይዞ ቦታው የኦሮሚያ ነው በሚል በ10 ኦሮሚያ ክልል ከተሞች ተቃውሞዎች ተቀስቅሰዋል።

የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ የተገነቡባቸው አካባቢዎች በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ሆነው የአዲስ አበባ መስተዳድር ውሳኔ የሚያሳልፈው እንዴት ነው፤ ለተፈናቃዮቹ አርሶ አደሮች የተሰጠው ካሳ እዚህ ግባ የማይባል ነው፤ የተቀናጀው ማስተር ፕላን ቅጥያ ነው የሚሉ ሀሳቦችን ተቃዋሚዎቹ አንስተዋል.
በምስራቅ ኦሮሚያ ጪሮ ከተማ ቢቢሲ ያነጋገረው አንድ ሰልፈኛ " በዚህ ተቃውሞ ላይ ዋነኛ መልዕክታችን በአዲስ አበባ አካባቢ ያሉት መሬቶች ለኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ሊመለስ ይገባል" የሚል ነው። ተቃዋሚው ጨምሮም ለብዙዎች ሞት ምክንያት የሆነው አወዛጋቢው የተቀናጀ ማስተር ፕላን ሊመለስ አይገባም ብሏል።
ተቃውሞዎቹ በሻሸመኔ፣ ጪሮ፣ ጂማ፣ አሰላ፣ አዳማና ሂርና ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የተስፋፉ ሲሆን በሻሸመኔ አካባቢ የሚገኙ ሰልፈኞች "ኦዲፒ ያልነውን ረስታችሁታል፤ መሬታችን የደም ስራችን ነው" የሚሉ መፈክሮችን ይዘው ነበር።
በትናንትናው ዕለት 51 ሺህ 229 የጋራ መኖሪያ ቤቶች በኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል የዕጣ ማውጫ ስነ ስርአት ለተጠቃሚዎች የተላለፈ ሲሆን፤ ከአካካቢው ለተነሱ አርሶ አደሮችና ልጆቻቸው ያለ እጣ እንዲሰጣቸው በከተማው አስተዳደር ካቢኔና በቤቶች አስተዳደር ውሳኔ መሰረት ያለ ዕጣ እንዲተላለፍ መወሰኑን ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ በትናንትናው ዕለት ገልፀዋል።
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ሲገነቡ የተጎዱ ሰዎች እንዳሉ ያልደበቁት ምክትል ከንቲባው "በተለይም የእርሻ መሬታቸውን ለነዚህ ተግባራት ሲሉ የለቀቁና ለኢኮኖሚና ማህበራዊ ቀውስ የተዳረጉ የአርሶ አደር ቤተሰቦችና ልጆቻቸው ህመማችሁ የእኛ መሆኑን እንድታውቁ" የሚል መልእክት አስተላልፈዋል።
ምክትል ከንቲባው ይህንን ቢሉም ኦሮሚያ ውስጥ ተቀስቅሶ ለረጅም ጊዜ ለዘለቀው ሕዝባዊ ተቃውሞ መነሻ ምክንያት እንደሆነ የሚነገርለትና ከ2006 ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ የነበረው የአዲስ አበባና በዙሪያዋ ያሉ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ ማስተር ፕላን ቅጥያ ነው የሚሉ ትችቶችም እየተሰሙ ነው።
ምንም እንኳን የተቀናጀው ማስተር ፕላን ከፍተኛ ተቃውሞዎችን ተከትሎ ውድቅ ቢደረግም የቀድሞው የአዲስ አበባ ከንቲባና ኦህዴድ ሊቀ መንበር አቶ ኩማ ደመቅሳ ጉዳዩ ከመፈናቀል ጋር አብሮ ስለመጣ እንጂ "ተራማጅ አስተሳሰብ ነው ብዬ አስባለሁ፤ ጊዜ ሊወስድ ይችላል እንጂ ማስተር ፕላኑ አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል" ብለው ለቢቢሲ መናገራቸው የሚታወስ ነው.
ምንም እንኳን ከመንግሥት በኩል ምንም አይነት መግለጫ ባይሰጥም በቅርቡ ከውጭ ሀገር የተመለሰው የተባበሩት ኦነግ በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ያለውን ድንበር መወሰን ያለበት የኦሮሚያ ክልል ነው የሚል ነው።
በ13ኛው ዙር የ20/80 ቤቶች 32ሺ 653 ቤቶችና በ2ኛ ዙር የ40/60 ቤቶች ለተጠቃሚዎች የሚተላለፉ ሲሆን፤ ከነዚህም ውስጥ 1ሺ 248 ስቱዲዮ፣ 18ሺ 823 ባለ አንድ መኝታ፣ 7ሺ 127 ባለሁለት መኝታ እና 5ሺ455 ደግሞ ባለ ሶስት መኝታ መሆናቸው ተገልጿል።
በ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውስጥ የሚካተቱትም በ1997 ተመዝግበው በ2005 ዓ.ም በነባር መደብ የተመዘገቡና በ2005 ዓ.ም የአዲስ ባለ ሶስት መኝታ ተመዝጋቢ ደንበኞች መሆኑ ተገልጿል።
Share:
Women's Fashion Category

Popular Posts

Blog Archive

Recent in Sports

3/recentposts
[recent]

Tags

Recent Comments

Recent Post

LightBlog

Recent

Adbox

Popular

Recent Posts