• This is default featured slide 1 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 2 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 3 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 4 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

  • This is default featured slide 5 title

    Go to Blogger edit html and find these sentences.Now replace these sentences with your own descriptions.This theme is Bloggerized by NewBloggerThemes.com.

በጦላይ የኦነግ ሠራዊት አባላት ላይ የተከሰተው ምንድን ነው ?

ከባለፈው እሁድ ጀምሮ የጤና እክል ገጥሟቸው ሆስፒታል እየገቡ ያሉ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ወታደሮች ቁጥር እየጨመረ ነው።
ወታደሮቹ ቁርስ ተመግበው ሲነሱ ብዙ እራሳቸውን እየሳቱ መውደቅ መጀመራቸው መነገሩ ይታወሳል። ወታደሮቹ ጨምረውም የቀረበላቸው ሻይ ውስጥ ነጭ ባዕድ ነገር መመልከታቸው እና የተለየ ጠረን እንዳለው ጨምረው ተናግረዋል።
"ሻይ በምንጠጣበት ብርጭቆ ስር ነጭ ዱቄት የሚመስል ነገር አግኝተናል፤ ይህንንም ለማሰልጠኛው አስተዳደሮች አሳይተናል" ሲል አንድ ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ የኦነግ ሠራዊት አባል ለቢቢሲ ተናግሯል።
የጤና እክል በገጠማቸው የሠራዊቱ አባላት ላይ የሚታዩበት ምልክት ምን እንደሆነ ሲናገር "የአፍ ድርቀት፣ የሆድ ቁርጠት፣ ሆድ የማቃጠል ስሜት፣ ከደም ጋር የተቀላቀለ ትውከትና የፊት መገርጣት ናቸው" ብሏል።
የኦሮሚያ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር የሆኑት ረታ በላቸው፤ በጦላይ በሚገኙ የኦነግ ወታደሮች ላይ ያጋጠመው የጤና ችግር መንስዔ እየተጣራ ነው ያሉ ሲሆን የደረሰባቸው የጤና እክል ግን ለህይወት አስጊ አይደለም ብለዋል።
እንደ ምክትል ኮሚሽነሩ ከሆነ 134 የኦነግ ወታደሮች በወሊሶ ቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደነበር ተናግረዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ የጦላይ ማሰልጠኛ አስተዳደሮች ጉዳት አስከተለ የተባለውን ሻይ ቀምሰው ምን የደረሰባቸው ነገር የለም ብለዋል። ''እኛ የቀረበላቸው ሻይ ውስጥ መርዝ ተጨምሯል ብለን አናምንም፤ ምርመራ እየተካሄደ ነው። እንደተባለው መርዝ ተጨምሮ ከተገኘ ግን ጠፋተኛው ላይ እርምጃ ይወሰዳል።''
በዚሁ ሆስፒታል እየታከመ የሚገኘው ሌላኛው የሠራዊቱ አባል ኢብሳ በበኩሉ የተሰጣቸውን ሁሉ ተመግበው ቢሆን ኖሮ ጉዳቱ ከፍ ያለ ሊሆን እንደሚችል ገልፆ "ሁላችንም እናልቅ ነበር" በማለት ተናግሯል።
"ይሄ ነገር የመርዝ ሽታ አለው ብዬ ስላስቆምኩዋቸው ሻዩን አልጨረሱትም ነበር። ገሚሱ ቀምሰው ብቻ ስለሆነ የተዉት በዚያ መንገድ ነው የተረፍነው" ይላል።
"እከሌ ብለን ማንም ላይ ጣታችንን ባንቀስርም ህብረታችንን የማይወዱ ሰዎች እንዳሉ እንጠረጥራለን። ነገር ግን ግቢው ውስጥ ካሉ ሰዎች ጋር ምንም አይነት ግጭት የለንም" ብሏል።
ወሊሶ በሚገኘው የቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል ሃኪም የሆኑት ዶ/ር አብዱላቲፍ ይሲያቅ እስከ ዛሬ ማክሰኞ ከሰዓት ድረስ 154 የኦነግ ሠራዊት አባላት ህክምና እየተደረጋለቸው መሆኑን ተናግረዋል።
"በእኛ ምርመራ መሰረት የምግብ መበከል (መመረዝ) ሳይሆን ራሱን የቻለ መርዝ ተጨምሮበት እንደሆነ ነው የሚያሳየው። የሠራዊቱ አባላትም መርዝ እንደሸተታቸው ተናግረዋል" ብለዋል።
ዶ/ሩ ጨምረውም ታካሚዎች ራስ ምታት፣ የሆድ ቁርጠት፣ ሆድ የማቃጠል ስሜት፣ ከደም ጋር የተቀላቀለ ትዉከትና የፊት መገርጣት ምልክቶች እንደታየባቸው በመናገር እነዚህም የመርዝ ምልክቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።
የክልሉ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው በበኩላቸው 136 የኦነግ ሠራዊት አባላት በጤና እክል ምክንያት በወሊሶ ሉቃስ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑንና የከፋ የጤና ችግርም እንደሌለ ለመንግሥት ሚዲያዎች በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
በመግለጫቸው ጨምረው በሠራዊቱ አባላት ላይ የምግብ መመረዝ ደርሶባቸዋል፤ ሠራዊቱ ላይም ይህ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው እየተባለ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው ብለዋል።
ያጋጠመውን የጤና እክል መንስኤም ለማጣራት ፖሊስና የሚመለከታቸው አካላት ምርመራ እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀው መንስኤውም ሲታወቅ ውጤቱ ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ነው
Source 
bbc
Share:

በወሲብ ፊልሞች ሱሰኛ የሆኑ ወጣት ሴቶች

ኔላም ቴለር የወሲብ ፊልሞችን ማየት የጀመረችው በ12 ዓመቷ ነበር። ገና አንድ ፍሬ ልጅ በምትባልበት ጊዜ። በመኝታ ክፍሏ ተደብቃ አጠር ያለ የአስር ደቂቃ የወሲብ ፊልም ማየት የጀመረችው በለጋ እድሜዋ ነው።

ኋላ ላይ እስከ አንድ ሰዓት ርዝማኔ ያላቸው ምስሎችን ማየት ጀመረች። በጊዜው ከቤተሰቦቿ ተደብቃ ታይ እንደነበር የምትናገረው ኔላም ለመጀመሪያ ጊዜ የወሲብ ፊልም ስታይ "የፍቅር ፊልሞች ወሲብን የተቀደሰና በፍቅር የተሞላ አድርገው ነበር አዕምሮዬ ላይ የሳሉት፤ ልክ በወንዶች ሃያልነት የተሞላና አካላዊ ተራክቦው የጎላበትን ምስል ማየት በጣም ነው ያስደነገጠኝ" ትላለች።
የወሲብ ምስሎችን ማየት የጀመረችበትን ሰበብ ስታስታውስ ጉዳዩን ለማወቅ ከነበራት ፍላጎት ወይም ለአቅመ-ሔዋን እየደረሰች ስለነበረ የአፍላ ጉርምስና ግፊት ይሆናል በማለት ትናገራለች።
ከጊዜ በኋላም የተለያዩ የወሲብ ምስሎችን ከማየቷ የተነሳ የራሷ ምርጫዎች እያዳበረች መጣች።
"ወጣት ሴቶች በዕድሜ ገፋ ካሉ ወንዶች ጋር ሆነው ለሚሰሩ የወሲብ ምስሎች ልዩ ስሜት አደረብኝ። ሴቶቹ ታዛዥ ሆነው ወንዶቹ የበላይ የሆኑባቸውን ምስሎች በ13 ዓመቴ መፈለግ ጀመርኩ" የምትለው ኔላም ይህ ፍላጎቷ ብዙ የወሲብ ምስል ከማየቷ የተነሳ ይሁን ወይም ተፈጥሯዊ የሆነ ስሜት መለየት ይከብዳታል።
የ25 ዓመቷ ሳራም ከኔላ የተለየ ልምድ የላትም። የወሲብ ምስሎችን ማየት የጀመረችው በ13 ዓመቷ ነበር፤ ለዚያውም በሳምንት ሁለት ጊዜ። 
እስካሁን የወሲብ ምስል ሱስ በወንዶች ላይ የሚያደርሰው ተፅዕኖ በደንብ የተጠና ሲሆን፤ በሴቶች ላይ ያለው ጫና ግን በውል አልተጠናም። ብዙ በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ ባለሙያዎች ሴቶች የወሲብ ምስልን እንደሱስ እንደማይጠቀሙትና በእነርሱ ላይ ብዙም ተፅዕኖ እንደሌለው ይናገራሉ። በዚህ የሕይወት መንገድ ላይ ያለፉ ሴቶች ግን ተመሳሳይ መልስ አይሰጡም።
ዶ/ር ለይላ ፈሮድሻ የፅንስና የማህፀን አማካሪ ስትሆን በ20 ዓመት የስራ ልምዷ "አንድም የማያቸው የወሲብ ምስሎች ችግር እየፈጠሩብኝ ነው" ብላ የመጣች ሴት አጋጥማት እንደማታውቅ ትናገራለች።
በጉዳዩም በደንብ ጥናት እንዳልተደረገበት የምትናገረው ለይላ "ሴቶች አካላዊና ስለ ልቦናዊ ጥቃት እየደረሰባቸው ነገርግን የሐኪም እርዳታ እየጠየቁ ስላልሆነ ነው? ወይስ ስለደረሰባቸው ችግር ለመናገር አፍረው? ወይስ ምንም ችግር እየፈጠረባቸው አይደለም?" በማለት ያልተመለሱ ጥያቄዎችን ታቀርባለች።
ኔላም 16 ዓመቷ ሲሆን የወሲብ ምስሎችን ማየት አቆመች፤ ለዚህ ደግሞ ሰበብ የሆናትን ስትጠቅስ ምስሎቹ ተፈጥሯዊ ያልሆነ ከፍተኛ ስሜት ውስጥ ስለሚከቱ ነው ትላለች። ከእውነታው እያራቀች እንደነበር የምትገልፀው ኔላም "የወሲብ ምስል አይቼ የማገኘው የስሜት እርካታና ከጓደኛዬ ጋር ከወሲብ በኋላ ያለኝ ስሜት ያላቸው ልዩነት ያስፈራኝ ነበር።"
አሜሪካዊቷ ፀሃፊ ኤሪካ ጋርዛ የወሲብ ምስል ማየት የጀመረችው በ12 ዓመቷ እንደሆነ ስትናገር "ትምህርት ቤት ያላግጡብኛል፤ ብዙ ጊዜም ብቸኛ ነበርኩ። ስለዚህም የወሲብ ምስሎችን ችግሬን የምረሳበትና እራሴን የማስደስትበት ነገር ነበር" ትላለች።
ኔላምም በተመሳሳይ መልኩ የወሲብ ምስሎችን በለጋ ዕድሜዎ ማየቷ ወሲብን የምታይበትን መንገድ እንደቀየረው ትናገራለች።
" 17 ወይም 19 እድሜዬ ላይ ስደርስ ታላቆቼ ከሆኑ ጋር ግንኙነት መፍጠር ጀመርኩ። ይህ ሁኔታዬ የተፈጥሮ ባህሪዬ ይሁን የወሲብ ምስል ማየቴ የፈጠረው ለማወቅ አልችልም" ትላለች።
እ.ኤ.አ በ2010 በተደረገ የ300 የወሲብ ምስሎች ግምገማ 88 በመቶ የሚሆኑት አንዱ ፆታ በወሲብ ላይ ያለውን የበላይነትን የሚያመላክቱ ሲሆን ብዙዎቹም የወንዶች የበላይነት ናቸው። በምስሎቹም ሴቶቹ በወንዶቹ ባህሪ በደስታ ወይም ከስሜት ነፃ በሆነ መልኩ እንደሚመልሱ ያሳያሉ
Share:

አደጋው የደረሰበት ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን የገጠመው ምንድን ነበር?

ከሦስት ሳምንታት በፊት አደጋ ስለደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎች እየወጡ ነው።

በዚህም በቦይንግ 737 ማክስ ላይ ያለው አውሮፕላኑ ዝግ እንዳይል ወይም እንዳይቆም የሚያደርገው የአውሮፕላኑ ሥርዓት የ157 ሰዎችን ህይወት ለቀጠፈው አደጋ ምክንያት እንደሆነ እየተነገረ ነው።
አደጋው ከመድረሱ በፊት በሁለቱ አብራሪዎች መካከል የተደረገን ምልልስ ጠቅሶ ዎል ስትሪት ጆርናል እንደዘገበው፤ የአውሮፕላኑ የሬዲዮ ግንኙነት ከመቋረጡ በፊት አንደኛው አብራሪ "ቀና አድርገው! ቀና አድርገው!" በማለት ለባልደረባው ሲናገር ተሰምቷል።
በአውሮፕላኑ ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመቆጣጠር ያስችላል የተባለውን ሥርዓት አብራሪዎቹ ቢጠቀሙም አደጋውን ለማስቀረት እንዳልተቻለ እየተደረገ ላለው ምርመራው ቅርብ የሆኑ ምንጮች ለጋዜጣው ተናግረዋል።
አደጋ ከደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን የበረራ መረጃ መሰብሰቢያ ሳጥን ውስጥ ከተገኘ የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ መሰረት አደጋው ከመድረሱ በፊት እያሽቆለቆለ ያለውን አውሮፕላን ሊታደግ ይችላል የተባለው የአውሮፕላኑ ሥርዓት እንዲሰራ ተደርጎ እንደነበር አመልክቷል።
ዘ ዎል ስትሪት ጆርናል የተባለው ጋዜጣ ስለአደጋው የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት ስማቸው ያልተጠቀሱ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው የአውሮፕላኑ ከፍታና ዝቅታ ለመቆጣጠር እንዲያስችል ተደርጎ የተሰራው የኮምፒውተር ሥርዓት ችግር እንዳለው አመልክቷል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን የበረራ ቁጥር ኢቲ302 መጋቢት 1/2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ጠዋት 2፡38 በመነሳት ሁለት ሰዓት ብቻ ለሚፈጀው በረራ ወደ ናይሮቢ ፊቱን ቢያዞርም ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ችግር ገጥሞታል።
አውሮፕላኑ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከተነሳ ከስድስት ደቂቃዎች በኋላም 48 ኪሎሜትሮችን ከአዲስ አበባ በስተደቡብ ምሥራቅ ተጉዞ ከቢሾፍቱ አቅራቢያ ባለችው ቱሉ ፈራ መንደር ውስጥ ነበር ወድቆ የተከሰከሰው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላኑ ዋና አብራሪ ያሬድ ጌታቸው ችሎታን በተመለከተ አብራሪው ከ8ሺህ ሰዓታት በላይ የማብረር ልምድ እንዳለው በመጥቀስ "የሚያስመሰግን ብቃት" አለው ብሏል።
አደጋው በደረሰበት ዕለትም አብራሪው ያሬድ ጌታቸው ችግር እንደገጠመውና ተመልሶ ለማረፍ ለበረራ ተቆጣጣሪዎች መልዕክት አስተላልፎ ነበር።
ከዚህ አደጋ ጋር በተያያዘ የአውሮፕላኑ የደህንነት መጠበቂያ ሥርዓት ለሚደረገው ምርምራ ዋነኛው ጉዳይ ሆኗል


Image copyrighከዚህ አደጋ ጋር በተያያዘ የአውሮፕላኑ የደህንነት መጠበቂያ ሥርዓት ለሚደረገው ምርምራ ዋነኛው ጉዳይ ሆኗል።

ኤምካስ የተባለውና አውሮፕላኑን በከፍተኛ ሁኔታ ወደላይ እንዳይወጣ ወይም ወደታች እንዳያሽቆለቁል ለመቆጣጠር እንዲቻል ተብሎ የተሰራ ሥርዓት ነው።
በአውሮፕላኑ ዝግ ሲል በትክክለኛው አቅጣጫ እንዲበር ለማስቻል የሚፈለገውን ኃይል ለማግኘት ወደ ላይ ወይም ቁልቁል በመሄድ ወደሚፈለገው ከፍታ ይመለሳል። ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን በአውሮፕላኑ ክንፎች በኩል ያለውን የመቆጣጠሪያ አቅም በመቀነስ አውሮፕላኑ እንዲወድቅ ሊያደርገው ይችላል።
በተለመደው ሁኔታ አውሮፕላኑን ከዝግታ ለማውጣት አብራሪው የአውሮፕላኑ አፍንጫ ወደታች እንዲያዘቀዝቅ ያደርጋል። አደጋው በደረሰበት ቦይንግ 737 ማክስ አይነት አውሮፕላኖች ላይ ያለው የመቆጣጠሪያ ሥርዓት (ኤምካስ) ግን እንዲህ አይነቱ ሁኔታ ሲከሰት አውሮፕላኑን እራሱ አስተካክሎ ወደ ትክክለኛው ቦታ ይመልሰዋል።
አውሮፕላኑ ላይ ተመሳሳይ ነገር የሚከሰት ከሆነና ኮምፒውተሩ ይህንኑ ካወቀ የመቆጣጠሪያ ሥርዓቱ በተደጋጋሚ የማስተካከያ እርምጃን በእራሱ ይወስዳል።
በኢትዮጵያው አየር መንገድ ላይ አደጋው ከመድረሱ አምስት ወራት ቀደም ብሎ ተመሳሳይ አደጋ የደረሰበት የኢንዶኔዢያው አውሮፕላንም የበረራውን ማዕዘን በሚያሰላው የአውሮፕላኑ መቆጣጠሪያ ላይ ተመሳሳይ አይነት እክል ገጥሞት እንደነበር ተገልጿል።
በቦይንግ ምስለ በረራ ላይ በተደረገ ሙከራ እንደተረጋገጠው ኤምካስ የተባለው መቆጣጠሪያ ከሚጠበቀው በላይ ከበድ ያለ በመሆኑ በተደጋጋሚ የአውሮፕላኑ አፍንጫ ቁልቁል እንዲያዘቀዝቅ ያስገድዳል።
በኢንዶኔዢያው አውሮፕላን ላይ የደረሰውን አደጋ ለማወቅ በተደረገው የምስለ በረራ ሙከራ ላይ እንደተደረሰበት አውሮፕላኑ ቁልቁል በአፍንጫው ባህር ላይ ሊከሰከስ መሆኑን ያወቁት ከ40 ሰከንዶች ያነሰ ጊዜ ሲቀራቸው መሆኑን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል።
ይህንንም ተከትሎ ቦይንግ ኤምካስን እንዴት መጠቀም እንደሚቻል ለአብራሪዎች መመሪያ ቢያወጣም፤ ነገር ግን በአውሮፕላኑ ላይ ያለውን ሥርዓት የሚቆጣጠረው ሶፍትዌር ላይ ያስፈልግ የነበረው መሻሻያ ዘግይቶ ባለፈው ሳምንት ነው ይፋ የተደረገው።
በተጨማሪም በበረራ ወቅት ችግር በሚያጋጥም ጊዜ አብራሪዎችን ሊያስጠነቅቅ ይችል የነበረው የማስጠንቀቂያ መብራትም አደጋው በደረሰባቸው ሁለቱ የኢትዮጵያ እና የኢንዶኔዢያ አውሮፕላኖች ላይ አልተገጠመም ነበር።
ከሁለቱ አደጋው ከደረሰባቸው አውሮፕላኖች የተገኙ የበረራ መረጃዎች ተመሳሳይነት እንዳላቸው መርማሪዎች አመልክተዋል።
የአውሮፕላኖቹን ወደ ላይ የመውጣትና የመውረድ ፍጥነት ንባብ እንደሚያመለክተው ሁለቱም አውሮፕላኖች ከፍና ዝቅ እያሉ እንደነበሩና አብራሪዎቹም ይህንን በመቆጣጠር አውሮፕላኖቹ ከፍ ብለው እንዲበሩ ጥረት ሲያደርጉ ነበር።
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ የትራንስፖርት ደህንነት ቦርድ ጋር በመሆን ምርመራውን እያካሄደ የሚገኘው የአሜሪካ የአየር ትራንስፖርት ባለስልጣን እንዳለው ከአደጋው ስፍራና ከሳተላይት የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ሁለቱ አውሮፕላኖች ላይ በጣም የሚመሳሰሉ ነገሮች እንደታዩ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን የበረራ መረጃ መመዝገቢያውና የአብራሪዎቹ ክፍል ድምጽ መቅጃው ወደ ፈረንሳይ ተወስዶ ምርመራ ተደርጎበታል።

ምንጭ .bbc
Share:
Women's Fashion Category

Popular Posts

Blog Archive

Recent in Sports

3/recentposts
[recent]

Tags

Recent Comments

Recent Post

LightBlog

Recent

Adbox

Popular

Recent Posts